SlideShare a Scribd company logo
1 of 3
Download to read offline
1
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አኃዱ አምላክ፤ አሜን።
ልደተ ክርስቶስ
የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላልፎ በሐጢያት ከወደቀ በኋላ እግዚአብሔር ወደ ቀደመ
ክብሩና ቦታው ይመልሰው ዘንድ በንሰሐ ወደፈጣሪው ቀረበ። አዳም እና ሔዋን ከገነት ከወጡ በኋላ
ለአርባ ቀናት ያህል ሱባዔ ገብተው ሳለ በ35 ኛው ቀን ከግማሽ ላይ ቀድሞ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ
እንዲያፈርሱ ያደረጋቸው ሰይጣን ዳግመኛ ወደ ሔዋን ቀርቦ ሔዋን ሆይ ጸሎታችሁ ተሰማ አዳምን
ይዘሽ ወደዚህ ነይ አላት። እርሷም በጎ መልአክ መስሎ የቀረበውን የጥንተ ጠላታቸውን ድምጽ ሰምታ
አዳምን ይዛ ከሱባኤያቸው ወጡ። በመንገድም ሲሄዱ በጎ መልአክ መስሎ የመጣው ዲያብሎስ አሁን
አገኘሁህ ከኔ አታመልጥም ብሎ አዳምን ድንጋይ አንስቶ ፈነከተውና ተሰወረ።
አዳምም በወደቀበት ደሙን እያዘራ ምርር ብሎ በማልቀስ ከዋለ ካደረ በኋላ እውነተኛው መልአክ
ቅዱስ ገብረኤል ተገልጾ አጽናናው። ፈጣሪ አምላክም የደረሰበትን ሁሉ አይቶ አዘነለት። ከወደቀበት
መከራም ሁሉ ያድነው ዘንድ ወዶ የተስፋ ቃል ሰጠው። ይህም የተስፋ ቃል ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ
መጥቼ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው የሚል ነበረ።
መልአኩም ቅዱስ ገብርኤል በል ተነስተህ ሔዋንን ያዝና ሂድ ብሎ አዘዘው። አዳም ግን ይህች ሴት
ሁለት ጊዜ ከፈጣሪዬ አጣላችኝ ከዚህ በኋላ ላያት አልፈልግም ብሎ እምቢ አለ። መላኩም አዳም ሆይ
ከወጣህበት ገነት የምትመለሰው ድህነትንም የምታገኘው በእርሷ በኩል ነውና ሔዋንን ይዘህ ሂድ
አለው። በዚህም ለሰዎች ድኅነትን የምታሰጥ የመድኃኒታቸው መገኛ የሆነች ዳግማዊት ሄዋን የተባለች
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የድህነታች መሠረት እንደሆነች ታወቀ።
ዳግመኛም አምላክ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው ያለውን የተስፋ ቃል አዳም በልቡ ሰንቆ መኖሩ
ያቺ የተስፋው ቃል ድንግል ማርያም እንደሆነች የተረዳ ነገር ሆነ። ሊቁ “አንቲሁ ተስፋሁ ለአዳም አመ
ይሰደድ እምገነት” በማለት እንደተናገረው ከገነት በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋው የሆነች ድንግል
ማርያም ናትና።
እንግዲህ ይህ የዘመን ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ የሰው ልጆችን ሊያድን ጌታችን እና አምላካችን መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ።
ከመወልዱ አስቀድሞ ከተወለደም በኋላ በምን ሁኔታ እንደሚጸነስ እና የት፣ ከማን፣ እንደምን ባለ
ሁኔታ እንደሚወለድ በአበውና በነብያት እንዲሁም በሃዋርያት መጽሐፍት ውስጥ ታርኩ በሰፊው
ተመዝግቦ ይገኛል። ከእነኝህ የመጽሐፍት ክፍሎች ውስጥ አብዛኛውን ለአንባብያን በመተው ጥቂቶቹን
ብቻ እንደሚከተለው እንመለከታለን።
በብሉይ ኪዳን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ/ሰው መሆን
የተነገሩ ኃይለ ቃላት ፦
2
1. ኦሪት ዘፍ. 22:8,13 “አብርሃምም። ልጄ ሆይ፥ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል
አለው፤ ሁለቱም አብረው ሄዱ። ... አብርሃምም ዓይኑን አነሣ፥ በኋላውም እነሆ አንድ በግ በዱር
ውስጥ ቀንዶቹ በዕፀ ሳቤቅ ተይዞ አየ፤ አብርሃምም ሄደ በጉንም ወሰደው፥ በልጁም ፋንታ
መሥዋዕት አድርጎ ሠዋው።”
2. ትንቢተ ሚል. 5:2 “አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል
ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ
የሚሆን ይወጣልኛል።”
3. ትንቢተ ኢሳ. 11:1 “ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል።”
4. ትንቢተ ኤር. 23:5 “ እነሆ፥ ለዳዊት ጻድቅ ቍጥቋጥ የማስነሣበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል
እግዚአብሔር፥ እርሱም እንደ ንጉሥ ይነግሣል፥ ይከናወንለታልም፥ በምድርም ፍርድንና ጽድቅን
ያደርጋል።”
5. ትንቢተ ኢሳ. 7:14 “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል
ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
6. መዝ. 72:9-10 “በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፥ ጠላቶቹም አፈር ይልሳሉ። የተርሴስና
የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ፤ የዓረብና የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ።”
7. መዝ. 2:7 “ትእዛዙን እናገራለሁ፤ እግዚአብሔር አለኝ። አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁህ።”
8. መዝ. 9:2,6 “ በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው።
.... ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤
ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።”
በአዲስ ኪዳን ስለ ክርስቶስ መወለድ/ ሰው መሆን የተጻፉ፦
1. ማቴ. 1:1 “ የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ”
2. ማቴ. 1:18 “ የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ
ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች”
3. ማቴ. 1፡20-23 “እርሱ ግን ይህን ሲያስብ፥ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው፥ እንዲህም አለ።
የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፥ ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ
አትፍራ።... ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን
ኢየሱስ ትለዋለህ። እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል
ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል
ነው። ”
3
4. ማቴ.2:1-2 “ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ
ሰገል። የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና
እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።”
5. ሉቃ.1 30-33 " መልአኩም እንዲህ አላት። ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና
አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።
እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን
ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም።”
6. “ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤
ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል”
7. ሉቃ. 2:6-14 “ በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥ የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥
በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም
አስተኛችው። በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ። እነሆም፥
የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ። መልአኩም
እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤
ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ይህም
ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ። ድንገትም ብዙ
የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ። ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም
ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”
8. ገላ. 4:4 “ ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም
በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤”
ወዳጆች ሆይ፤ እኒህን ሁሉ የእግዚአብሔር ቃሎች አምነን የጌታን ልደት ስናከብር ድርሻችን ታሪኩን
ማወቅና በእግዚአብሔር ልጅ ማመን ብቻ ሳይሆን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወዚህ ዓለም የመጣበትን
ዋነኛውን ዓላማ ፈጽመን እንድንገኝም ጭምር ነው። ይኽውም ከሃጢያትና በደል እርቀን ብርሃን የሆነንን
ክርስቶስን ለብሰን ዘወትር ዝግጁ በመሆን የዘላለም ሕይወትን ለመውረስ የበቃን እንድንሆን ነው። የጌታን
ልደት የምናከብርበት የገና በአል ዘወትር በየአመቱ ሲመላለስ እኛም ዘወትር በንሰሐ እየታደስን በቅዱስ
ሥጋውና በክቡር ደሙ በመወሰን አዲስ ሕይወትና አዲስ መንፈስ ሊኖረን ይገባል። ነብዩ ““ አዲስ ልብና
አዲስ መንፈስ ለእናንተ አድርጉ :: ብሎ እንደነገረን ” ሕዝ. 18፥31
መልካም በአል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር።

More Related Content

What's hot

وسائل -تحصين-الانسان - جزء -أول
وسائل -تحصين-الانسان - جزء -أولوسائل -تحصين-الانسان - جزء -أول
وسائل -تحصين-الانسان - جزء -أولyahyaislam
 
Psalms book 4: Wandering songs for the travels and travails of life
Psalms book 4:  Wandering songs for the travels and travails of lifePsalms book 4:  Wandering songs for the travels and travails of life
Psalms book 4: Wandering songs for the travels and travails of lifeMichael Scaman
 
أعمال الخزانات - Tanks Works
أعمال الخزانات - Tanks Works أعمال الخزانات - Tanks Works
أعمال الخزانات - Tanks Works Hussain Sbetan
 
Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)
Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)
Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)Boruj Krasniker
 
Deborah ዲቦራ - Amharic sermon,
Deborah ዲቦራ - Amharic sermon, Deborah ዲቦራ - Amharic sermon,
Deborah ዲቦራ - Amharic sermon, Operation Ezra
 
الجزء8 جامع القراءات
الجزء8 جامع القراءاتالجزء8 جامع القراءات
الجزء8 جامع القراءاتسمير بسيوني
 
قصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوين
قصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوينقصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوين
قصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوينFreekidstories
 
آيات - الشفاء - والسكينة - والحفظ
آيات - الشفاء - والسكينة - والحفظآيات - الشفاء - والسكينة - والحفظ
آيات - الشفاء - والسكينة - والحفظyahyaislam
 
ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdf
ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdfከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdf
ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdfssuser0a3463
 
Palestine 8 facts حقائق بسيطة عن فلسطين
Palestine 8 facts  حقائق بسيطة عن فلسطين Palestine 8 facts  حقائق بسيطة عن فلسطين
Palestine 8 facts حقائق بسيطة عن فلسطين Baker AbuBaker
 
2 sourat al fatiha wa al bakara
2 sourat al fatiha wa al bakara2 sourat al fatiha wa al bakara
2 sourat al fatiha wa al bakaraalaouiouafa
 
Parashah #7 vayetse
Parashah #7 vayetseParashah #7 vayetse
Parashah #7 vayetseantso
 
تاريخ فلسطين
تاريخ فلسطينتاريخ فلسطين
تاريخ فلسطينbasheer777
 
Daniel8 the cleansing of the sanctuary
Daniel8   the cleansing of the sanctuaryDaniel8   the cleansing of the sanctuary
Daniel8 the cleansing of the sanctuaryGod Is Love
 

What's hot (20)

وسائل -تحصين-الانسان - جزء -أول
وسائل -تحصين-الانسان - جزء -أولوسائل -تحصين-الانسان - جزء -أول
وسائل -تحصين-الانسان - جزء -أول
 
The God Who Fights for You - Joshua 10-12
The God Who Fights for You - Joshua 10-12The God Who Fights for You - Joshua 10-12
The God Who Fights for You - Joshua 10-12
 
Psalms book 4: Wandering songs for the travels and travails of life
Psalms book 4:  Wandering songs for the travels and travails of lifePsalms book 4:  Wandering songs for the travels and travails of life
Psalms book 4: Wandering songs for the travels and travails of life
 
أعمال الخزانات - Tanks Works
أعمال الخزانات - Tanks Works أعمال الخزانات - Tanks Works
أعمال الخزانات - Tanks Works
 
Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)
Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)
Rezo especial para los hijos por Rosh Jodesh Sivan (Español)
 
Ya ebnat daoud
Ya ebnat daoudYa ebnat daoud
Ya ebnat daoud
 
Deborah ዲቦራ - Amharic sermon,
Deborah ዲቦራ - Amharic sermon, Deborah ዲቦራ - Amharic sermon,
Deborah ዲቦራ - Amharic sermon,
 
الجزء8 جامع القراءات
الجزء8 جامع القراءاتالجزء8 جامع القراءات
الجزء8 جامع القراءات
 
قصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوين
قصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوينقصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوين
قصص من ﺍﻋﻤﺎﻝ ﺍﻟﺮﺳﻞ للأطفال - كتاب التلوين
 
آيات - الشفاء - والسكينة - والحفظ
آيات - الشفاء - والسكينة - والحفظآيات - الشفاء - والسكينة - والحفظ
آيات - الشفاء - والسكينة - والحفظ
 
ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdf
ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdfከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdf
ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ ያፈነገጡ አስተሳሰቦችና መልሶቻቸው.pdf
 
Palestine 8 facts حقائق بسيطة عن فلسطين
Palestine 8 facts  حقائق بسيطة عن فلسطين Palestine 8 facts  حقائق بسيطة عن فلسطين
Palestine 8 facts حقائق بسيطة عن فلسطين
 
2 sourat al fatiha wa al bakara
2 sourat al fatiha wa al bakara2 sourat al fatiha wa al bakara
2 sourat al fatiha wa al bakara
 
The Book of Acts: Chapter 7
 The Book of Acts: Chapter 7 The Book of Acts: Chapter 7
The Book of Acts: Chapter 7
 
Parashah #7 vayetse
Parashah #7 vayetseParashah #7 vayetse
Parashah #7 vayetse
 
Homiletic.pptx
Homiletic.pptxHomiletic.pptx
Homiletic.pptx
 
تاريخ فلسطين
تاريخ فلسطينتاريخ فلسطين
تاريخ فلسطين
 
The heavens and their hosts.
The heavens and their hosts.The heavens and their hosts.
The heavens and their hosts.
 
Como se sale de adulam
Como se sale de adulamComo se sale de adulam
Como se sale de adulam
 
Daniel8 the cleansing of the sanctuary
Daniel8   the cleansing of the sanctuaryDaniel8   the cleansing of the sanctuary
Daniel8 the cleansing of the sanctuary
 

More from University of Gondar (20)

Optical management of strabismus.pptx
Optical management of strabismus.pptxOptical management of strabismus.pptx
Optical management of strabismus.pptx
 
Spectacle and electronic magnifiers.pptx
Spectacle and electronic magnifiers.pptxSpectacle and electronic magnifiers.pptx
Spectacle and electronic magnifiers.pptx
 
Third nerve palsy.pptx
Third nerve palsy.pptxThird nerve palsy.pptx
Third nerve palsy.pptx
 
Vulnerable groups .pptx
Vulnerable groups .pptxVulnerable groups .pptx
Vulnerable groups .pptx
 
Complications of Trabeculectomy.pptx
Complications of Trabeculectomy.pptxComplications of Trabeculectomy.pptx
Complications of Trabeculectomy.pptx
 
Retina
RetinaRetina
Retina
 
Cornea
Cornea Cornea
Cornea
 
Anisometropia
AnisometropiaAnisometropia
Anisometropia
 
Ocular manifestations of HIV
Ocular manifestations of HIV Ocular manifestations of HIV
Ocular manifestations of HIV
 
eyelid anatomy slideshare
eyelid anatomy slideshareeyelid anatomy slideshare
eyelid anatomy slideshare
 
Lacrimal system ppt.
Lacrimal system ppt.Lacrimal system ppt.
Lacrimal system ppt.
 
ocular anatomy
ocular anatomyocular anatomy
ocular anatomy
 
Eye lid disorders
Eye lid disorders Eye lid disorders
Eye lid disorders
 
PRECED/PROCEED MODEL
PRECED/PROCEED MODEL PRECED/PROCEED MODEL
PRECED/PROCEED MODEL
 
Intelligence quotient
Intelligence quotient Intelligence quotient
Intelligence quotient
 
health and behavior
health and behavior  health and behavior
health and behavior
 
Disorders of the eye
Disorders of the eyeDisorders of the eye
Disorders of the eye
 
Global initiatives for blindness
Global initiatives for blindness Global initiatives for blindness
Global initiatives for blindness
 
Strabismic ambylopia
Strabismic ambylopia Strabismic ambylopia
Strabismic ambylopia
 
Physiology of the eye
Physiology of the eye Physiology of the eye
Physiology of the eye
 

ልደተ ክርስቶስ

  • 1. 1 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አኃዱ አምላክ፤ አሜን። ልደተ ክርስቶስ የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ተላልፎ በሐጢያት ከወደቀ በኋላ እግዚአብሔር ወደ ቀደመ ክብሩና ቦታው ይመልሰው ዘንድ በንሰሐ ወደፈጣሪው ቀረበ። አዳም እና ሔዋን ከገነት ከወጡ በኋላ ለአርባ ቀናት ያህል ሱባዔ ገብተው ሳለ በ35 ኛው ቀን ከግማሽ ላይ ቀድሞ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ እንዲያፈርሱ ያደረጋቸው ሰይጣን ዳግመኛ ወደ ሔዋን ቀርቦ ሔዋን ሆይ ጸሎታችሁ ተሰማ አዳምን ይዘሽ ወደዚህ ነይ አላት። እርሷም በጎ መልአክ መስሎ የቀረበውን የጥንተ ጠላታቸውን ድምጽ ሰምታ አዳምን ይዛ ከሱባኤያቸው ወጡ። በመንገድም ሲሄዱ በጎ መልአክ መስሎ የመጣው ዲያብሎስ አሁን አገኘሁህ ከኔ አታመልጥም ብሎ አዳምን ድንጋይ አንስቶ ፈነከተውና ተሰወረ። አዳምም በወደቀበት ደሙን እያዘራ ምርር ብሎ በማልቀስ ከዋለ ካደረ በኋላ እውነተኛው መልአክ ቅዱስ ገብረኤል ተገልጾ አጽናናው። ፈጣሪ አምላክም የደረሰበትን ሁሉ አይቶ አዘነለት። ከወደቀበት መከራም ሁሉ ያድነው ዘንድ ወዶ የተስፋ ቃል ሰጠው። ይህም የተስፋ ቃል ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ መጥቼ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው የሚል ነበረ። መልአኩም ቅዱስ ገብርኤል በል ተነስተህ ሔዋንን ያዝና ሂድ ብሎ አዘዘው። አዳም ግን ይህች ሴት ሁለት ጊዜ ከፈጣሪዬ አጣላችኝ ከዚህ በኋላ ላያት አልፈልግም ብሎ እምቢ አለ። መላኩም አዳም ሆይ ከወጣህበት ገነት የምትመለሰው ድህነትንም የምታገኘው በእርሷ በኩል ነውና ሔዋንን ይዘህ ሂድ አለው። በዚህም ለሰዎች ድኅነትን የምታሰጥ የመድኃኒታቸው መገኛ የሆነች ዳግማዊት ሄዋን የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የድህነታች መሠረት እንደሆነች ታወቀ። ዳግመኛም አምላክ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው ያለውን የተስፋ ቃል አዳም በልቡ ሰንቆ መኖሩ ያቺ የተስፋው ቃል ድንግል ማርያም እንደሆነች የተረዳ ነገር ሆነ። ሊቁ “አንቲሁ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት” በማለት እንደተናገረው ከገነት በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋው የሆነች ድንግል ማርያም ናትና። እንግዲህ ይህ የዘመን ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ የሰው ልጆችን ሊያድን ጌታችን እና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ። ከመወልዱ አስቀድሞ ከተወለደም በኋላ በምን ሁኔታ እንደሚጸነስ እና የት፣ ከማን፣ እንደምን ባለ ሁኔታ እንደሚወለድ በአበውና በነብያት እንዲሁም በሃዋርያት መጽሐፍት ውስጥ ታርኩ በሰፊው ተመዝግቦ ይገኛል። ከእነኝህ የመጽሐፍት ክፍሎች ውስጥ አብዛኛውን ለአንባብያን በመተው ጥቂቶቹን ብቻ እንደሚከተለው እንመለከታለን። በብሉይ ኪዳን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ/ሰው መሆን የተነገሩ ኃይለ ቃላት ፦
  • 2. 2 1. ኦሪት ዘፍ. 22:8,13 “አብርሃምም። ልጄ ሆይ፥ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል አለው፤ ሁለቱም አብረው ሄዱ። ... አብርሃምም ዓይኑን አነሣ፥ በኋላውም እነሆ አንድ በግ በዱር ውስጥ ቀንዶቹ በዕፀ ሳቤቅ ተይዞ አየ፤ አብርሃምም ሄደ በጉንም ወሰደው፥ በልጁም ፋንታ መሥዋዕት አድርጎ ሠዋው።” 2. ትንቢተ ሚል. 5:2 “አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል።” 3. ትንቢተ ኢሳ. 11:1 “ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል።” 4. ትንቢተ ኤር. 23:5 “ እነሆ፥ ለዳዊት ጻድቅ ቍጥቋጥ የማስነሣበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፥ እርሱም እንደ ንጉሥ ይነግሣል፥ ይከናወንለታልም፥ በምድርም ፍርድንና ጽድቅን ያደርጋል።” 5. ትንቢተ ኢሳ. 7:14 “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” 6. መዝ. 72:9-10 “በፊቱም ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ፥ ጠላቶቹም አፈር ይልሳሉ። የተርሴስና የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ፤ የዓረብና የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ።” 7. መዝ. 2:7 “ትእዛዙን እናገራለሁ፤ እግዚአብሔር አለኝ። አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁህ።” 8. መዝ. 9:2,6 “ በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው። .... ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።” በአዲስ ኪዳን ስለ ክርስቶስ መወለድ/ ሰው መሆን የተጻፉ፦ 1. ማቴ. 1:1 “ የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ” 2. ማቴ. 1:18 “ የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች” 3. ማቴ. 1፡20-23 “እርሱ ግን ይህን ሲያስብ፥ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው፥ እንዲህም አለ። የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፥ ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ።... ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ። እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው። ”
  • 3. 3 4. ማቴ.2:1-2 “ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል። የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።” 5. ሉቃ.1 30-33 " መልአኩም እንዲህ አላት። ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም።” 6. “ ይህም ከላይ የመጣ ብርሃን በጐበኘበት በአምላካችን ምሕረትና ርኅራኄ ምክንያት ነው፤ ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል” 7. ሉቃ. 2:6-14 “ በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥ የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው። በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ። እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ። መልአኩም እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ። ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ። ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።” 8. ገላ. 4:4 “ ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤” ወዳጆች ሆይ፤ እኒህን ሁሉ የእግዚአብሔር ቃሎች አምነን የጌታን ልደት ስናከብር ድርሻችን ታሪኩን ማወቅና በእግዚአብሔር ልጅ ማመን ብቻ ሳይሆን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወዚህ ዓለም የመጣበትን ዋነኛውን ዓላማ ፈጽመን እንድንገኝም ጭምር ነው። ይኽውም ከሃጢያትና በደል እርቀን ብርሃን የሆነንን ክርስቶስን ለብሰን ዘወትር ዝግጁ በመሆን የዘላለም ሕይወትን ለመውረስ የበቃን እንድንሆን ነው። የጌታን ልደት የምናከብርበት የገና በአል ዘወትር በየአመቱ ሲመላለስ እኛም ዘወትር በንሰሐ እየታደስን በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ በመወሰን አዲስ ሕይወትና አዲስ መንፈስ ሊኖረን ይገባል። ነብዩ ““ አዲስ ልብና አዲስ መንፈስ ለእናንተ አድርጉ :: ብሎ እንደነገረን ” ሕዝ. 18፥31 መልካም በአል። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር።