ጳጉሜን ለኢትዮጵያ.pptx
- 2. መ ግ ቢ ያ
አዲስ ዓመት ለኢትዮጵያውያን የብሩህ ተስፋ ጅማሮ፣ የተስፋ ስንቅ የምንሰንቅበት
ልዩ ሰሜትን የሚፈጥርልን ሲሆን ክብረ በዓሉም በጋራ የምናከብረው ለየት ያለ
መገለጫችን ነው፡፡
እንደሚታወቀው እየተገባደደ ባለው 2015 ዓ.ም በከተማችን አዲስ አበባ ህዝባችንን
ትርጉም ባለው ሁኔታ የሚቀይሩ በርካታ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው
አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በአገልግሎትም ቢሆን ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች
ቢኖሩም የመንግስት የመፈፀም አቅም ከአዳጊ የህዝብ ፍላጎት አንፃር አሁንም ቀሪ
የቤት ስራ እንዳለብን ይታመናል፡፡
በዚህም ጳጉሜ በኢትዮጵያ በሚል መሪቃል የምናከብራቸው ኩነቶችና እና መረሀ ግብሮች
ውጤታማነት እና ፋይዳ ተገምግሞ ለመጪው ዓመት አፈፃፀማችን ግብዓት በሚሆንበት
ሁኔታ የአገልግሎት ቀን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማከናወን እንዲቻል ይህ አጭር እቅድ
ተዘጋጅቷል፡፡
- 3. አስፈላጊነት
የጳጉሜን ወር የሚያልፈው ዓመት መጨረሻና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ናት፡፡
ኃላፊውን ዓመት በምስጋና በመሸኘት አዲሱን ዓመት በተስፋ ለመቀበል ምቹ
ወቅት ናት፡፡ በመሆኑም የከተማችንን የአገልግሎት አሰጣጥ ስኬታማ ለማድረግ
ብሎም በፐብሊክ ሰርቪሱ ውስጥ የአገልጋይነት መንፈስ በመላበስ
ህብረተሰባችን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ቃላችንን ዳግም የምናድስበት
እና ሀገራዊ የአገልግሎት አሰጣጥ መነቃቃት ለመፈጠር በተለያዩ ዝግጅቶች
የአገልግሎት ቀን ማክበር አስፈላጊ በመሆኑ ነው፡፡
- 4. ወሰን
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት እና
በግል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ተገልጋዩን
ህብረተሰብ ያማከለ ሆኖ ከማዕከል እስከ ወረዳ
ባሉ መዋቅሮች ተፈጻሚ ይሆናል።
ዓላማ
የአገልጋዩን የአገልጋይነት መንፈስ
ማዳበር እና የተገልጋዩን ህብረተሰብ
እርካታ በማጎልበት ለአዲሱ
አመት ጉዟችን ምቹ መደላድል
ለመፍጠር ነው፡፡
- 5. መሰረታዊ ሀሳብ
ከተማችማን አዲስ አበባ ከአፍሪካ ህብረት መቀመጫነት እስከ አለም
አቀፍ የዲፕሎማቶቸ መንደርነት የተጎናፀፈችና በመጎናጸፍ ላይ የምትገኝ
የመሆንዋ ሚስጥር የከተማዉ ማህበረሰብ አብሮነት እና አንድነትን
የተጎናጸፈው የሀገር ወዳድነት ዉጤት መሆኑ አይካድም፡፡ የበርካታ ብሄር
ብሄረሰብ እና ህዝቦች በመሥዋዕት የገነቧት እና የበርካታ እምነት
ተከታዮች የአብሮነት መለያን ተላብሰው በበጎነት የተጋመዱ በመሆናቸው
ክፋት እና ሌሎች ተግዳሮቶችን በአንደነት መክተዉ አዲስ አበባን ዉብና
ለሰዉ ልጅ ተስማሚ ከማድረግ ባሻገር ልማት ላይ አተኩረው በፍጥነት
በመጓዝ የከተማዋን ሁለንተናዊ ገፅታ በመገንባት ዛሬ ደርሰናል ፡፡
በቀጣይም የከተማችንን ዘርፋ ብዙ ዕቅድ ከስኬት ማድረስ የሚቻለዉ
ከወትሮ በላቀ አግባብ በአብሮነትና በመሥዋዕትነት ለልማት ቆርጦ
በመነሳት በመሆኑ የላቀ ምርታማነትን ለማምጣት አዳዲስ የስኬት
ምዕራፍ ስንጀምር ሀገር ወዳድ ትውልድን መገንባትን መሰረት ማድረግ
እንዳለብን በመረዳት ነው፡፡ በከተማችን ባሉት ሁሉም ማዕዘናት በደስታ
እና በሃዘናችን፤ በብርታት እና በድካማችን ቀን ከሌት የሚታየው ሀገር
ወዳድነታችን ዋጋው
ትልቅ ከመሆኑ ሊጠፋ የማይችል እና ከፍተኛ መሥዋዕትነት የተከፈለበት
በመሆኑ ለሁሉም የሚያበራ ብርሃናችን ነው፡፡
- 6. ከአመት አመት ያለው የአዲስ አመት አከባበር
እድገት
2013፡
አዲስ አበባን….
በአዲስ የተስፋ
ብርሃን
2014፡
አዲስ የኢትዮጵያ
የድል ነፀብራቅ
2015፡
አዲስ ሁለንተናዊ
ከፍታ
2016፡
ጳጉሜን ለኢትዮጵያ
ከተስፋ
ድል
ከፍታ
ሀገር
- 7. የቀናት ስያሜዎች
ጳጉሜ 1
የአገልጋይነት ቀን
ጳጉሜ 2
የመሥዋዕትነት ቀን
ጳጉሜ 3
የበጎነት ቀን
ጳጉሜ 4፡-
የአምራችነት ቀን
ጳጉሜ 5
የትውልድ ቀን
ጳጉሜ 6
አብሮነት ቀን
- 8. ጳጉሜን 1 የአገልግሎት ቀን
መሰረታዊ ሀሳብ
ማገልገል ከምንም በላይ ክቡር የሆነ ተግባር ነው። አገልግሎት ሁሉ ሰው እድሜውን ሁሉ
እየሰጠ እና እየተቀበለ የኖረበት የህይወት አካል ነው። አገልጋይነት በእውነት ለገባው ትንሽ
ትልቅ የማይባል፤ ከደሳሳ ቤት ጀምሮ እስከ ቤተ መንግስት ያለ የነበረ እና ወደፊትም
የሚኖር ታላቅ ተግባር ሲሆን መርሁም ታማኝነት ቅንነት እና አክብሮት ነው። ይህ ታላቅ
ተግባር አንዱ ማንነታችን ነውና በዚህ ቀን ይወደሳል፤ አገልግሎት የሚሰጠውም ክብር
ይሰጠዋል። እናም ከከተማዉ ከፍተኛ አመራሮች እስከ ባለሙያ ያሉት አካላት
ማህበረሰባችንን የማገልገል ስሜት በተላበሰ አግባብ ቅንና ትሁት በመሆን የማስተናገድና
የአገልጋይነት መንፈስ በተላበሰ መንገድ በቀጣይም መዝለቅ በሚችል አካኋን ይተገበራል።
- 9. የአገልጋይነት ቀን ላይ የሚተገበሩ መሰረታዊ ተግባራት
•በትራንስፖርት ተቅዋማት በመንግስትና በግል ተሽከርካሪዎች
ትህትናን በተላበሰ መነገድ ተሳፋሪን እንዲያገለግሉ ይደረጋል፣ታክሲ
ተራ አስከባሪዎችና የባስ ሾፌሮችን የሚያካትት ይሆናል።
የአገልጋይነት ተምሳሌት የሆኑት የጤና ባለሙያዎች፣ መምህራን፣
የፅዳት ሰራተኞች፣ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች፣ ኪነጥበብ፣
በጎ ፈቃድ ወዘተ በየዘርፋቸው ልዩ እውቅና በተቋማት የሚሰጥ
ይሆናል።
•በስራ ባህልና ክብር ዙሪያ ባህል ዙሪያ የማነቃቂያ ስልጠናና
ውይይት ይዘጋጃል።
የሚድያ
ስራዎቸ
•አገልጋይነትን
በተመለከተ
የአንድ ደቂቃ
የቴሌቭዥን
ማስታወቅያ
ስፖት
ይዘጋጃል።
- 10. •የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ፕሮጀክቶች ምርቃት
•በምን ልታዘዝ ስሜት በግልም ሆነ በመንግስት ተቃማት እለቱን
በተለየ ትህትና በማገልገልና የተገልጋይ እርካታን ባስመሰከረ
መንገድ ይተገበራል፤ በካፍቴሪያ፤ በተለያዩ ተቐማት ወዘተ።
•በዚህ ቀን በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ህዝብን ማገልገል ምን
ማለት እንደሆነ ይገለጣል፤
•በአገልግሎት ላይ ያጋጠሙ ፈተናዎችና መፍትሔያቸው ይነገራሉ፤
•የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት መደረግ ስላለባቸው ነገሮች አዳዲስ
ሐሳቦች ይቀርባሉ፤
•ከአገልግሎት ፈላጊው ማኅበረሰብ የሚጠበቁ ነገሮች ይነገራሉ፤
•ለቅን አገልጋዮች ምስጋና ይቀርባል፤
የሚድያ
ስራዎቸ
•አገልጋይነትን
በተመለከተ
የአንድ ደቂቃ
የቴሌቭዥን
ማስታወቅያ
ስፖት
ይዘጋጃል።
- 11. የአገልግሎት ቀን፤ ጳጉሜን አንድ(ረቡዕ)፡- በተለያዩ መንግሥታዊ የአገልግሎት
መስኮች የሚሳተፉ የሲቪል ሰርቪስና ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጪ አካላትን የተመለከተ
ቀን ነው፡፡
o በዚህ ቀን ሀገርን ማገልገልና ሕዝብን ማገልገል ምን ማለት እንደሆነ ይገለፃል፤
o በአገልግሎት ላይ ያጋጠሙ ፈተናዎችና መፍትሔያቸው ይነገራሉ፤
o የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት መደረግ ስላለባቸው ነገሮች አዳዲስ ሐሳቦች ይቀርባሉ፤
o ከአገልግሎት ፈላጊው ማኅበረሰብ የሚጠበቁ ነገሮች ይነገራሉ፤
ለቅን አገልጋዮች ምስጋና ይቀርባል፤
- 12. የአገልግሎት ቀን የሚከናወኑ ዋና
ዋና ተግባራት
ግብ 1፡- የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን በውጤታማነት ማጠናቀቅ
ግብ 2፡- ስራ ላይ ካሉ ሰራተኞች በተጨማሪ እረፍት ላይ ያሉ ሰራተኞች
እንዲገቡ በማድረግ እና ምቹ ሁኔታ መፍጠር{ግቢና የስራ ቦታ ማፀዳት እና
ምቹ ሁኔታ መፍጠር}
ግብ 3፡- የመንግስትና የግል ትራንፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ለአንድ ቀን
አገልግሎታቸውን በነጻ እንዲሰጡ ይደረጋል፡፡
ግብ 4፡- ጠዋት ሰንደቅ አላማ በጋራ ብሄራዊ መዝሙራችን በመዘመር
ይሰቀላል ማታ በጋራ ብሄራዊ መዝሙር በመዘመር ይወርዳል
ግብ 5፡- ከተቋማት የስራ ባህሪ አኳያ መስክ የሚያስኬድ ስራ ካለ የመስክ
ጉብኝት ማድረግ በዛም አገልግሎት መስጠት
- 13. የአገልግሎት ቀን የሚከናወኑ ዋና
ዋና ተግባራት የቀጠለ ……..
ግብ 6፡- አገልግሎት በተመለከተ ሰነድ አዘጋጅቶ ለተገልጋይና
ለአገልጋዬች አጭር ማብራሪያ መስጠት{ከአንድ ቀን ቀደም
ብሎ በ30/12/2015 }
ግብ 7፡- ባህላዊ አለባበስ ብዝሀነታችን እና የመደመር ትውልድ
በሚገልፅ መልኩ ማከናወን
ተግባር 1፡- ብዝሀነታችን በሚገልፅ መልኩ የብሄር ብሄረሰቦች አልባሳት መልበስ፣
ተግባር 2፡- ህብረብሄራዊ አንድነታችን የሚያጠናክሩ እሴቶች ጎልተው እንዲወጡ ማድረግ
ተግባር 3፡- አሳታፊነት ባለው መልኩ የሚከበር ይሆናል
ተግባር 4፡- ስራ ክቡር መሆኑ በሚያንፀባርቅ መልኩ
ተግባር 5፡- በመከባበርና በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ
ተግባር 6፡- የመደመር ትውልድ እሳቤዎችን የሚያጎለብቱ ክንውኖች ማካሄድ
- 14. የአገልግሎት ቀን የሚከናወኑ ዋና
ዋና ተግባራት የቀጠለ ……..
ግብ 8፡- በጡረታ የተገለሉና ጠንካራ ሰራተኞች የማበረታቻ
ስራ ይሰራል
ግብ 9፡- የአገልግሎት ቀን በህዝብ ግንኙነት ስራዎች ማጀብ
ግንዛቤ ሊያስጨብጡ፣ አመለካከት ሊለውጡ፣ አዳዲስ
አሠራር ሊያመጡ፣ ማኅበረሰቡን ሊያነሣሱ በሚችሉ
መልኩ ይቀረጻሉ፤
- 15. የኮሚቴ አደረጃጀት
የአብይ ኮሚቴ አባላት
1. ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሰብሳቢ
2. የትራንስፖርት ቢሮ አባል
3. የባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ አባል
4. የጤና ቢሮ አባል
5. የከንቲባ ፅ/ቤት አባል
6. ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አባል
7. የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች ኤጀንሲ አባል
8. ኮሙኒኬሽን ቢሮ አባል
- 16. የማስፈፀሚያ ስልቶች
መልዕክቶች ወጥነት ባለዉ አግባብ ይተላለፋሉ፣
የአገልግሎት ቀን ተግባራትን በመገምገም አቅጣጫ
እየተቀመጠ እንዲሄድ ይደረጋል፣
ሁሉም የኮሙኒኬሽን አግባቦች ተግባራዊ ይደረጋሉ፣
ከማዕከል እስከ ወረዳ እንዲሁም ከሴክተሮች ጋር
በመቀናጀትና በመናበብ የሚተገበር ይሆናል፣
ሥራውን ከሚያስተባብረው የከተማው ኮሚቴ ጋር
በመቀናጀት አፈፃፀሙን ይከታተላል፣
- 17. የማስፈፀሚያ ስልቶች የቀጠለ…
በየደረጃ ያሉ አመራርና ሠራተኞች ለተልዕኮው ውጤታማነት
በቅንጅት የሚሰሩ ይሆናል፡፡
የሰለቹና ተመሳይነት ያላቸው ፕሮግራሞች እንዳይነደፉ
ማድረግ ያስፈልጋል፤
ፕሮግራሞቹ ለሚዲያ ተስማሚ እንዲሆኑ የሚዲያ አጋሮች
ከመነሻ እስከ መጨረሻው አብረው የኮሚቴ አባል ሆነው
ይሠራሉ፤
በየዕለቱ የሚደረጉትን መርሐ ግብሮች ሁሉም የሀገሪቱ
ሚዲያዎች በተመቻቸው መንገድ ያስተላልፋሉ፤
ነሐሴ 26 ቀን 2015፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ
ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ስለ ጳጉሜን 1
የአገልግሎት ቀን አከባበር ዝርዝር መግለጫ ይሰጣሉ፤
- 18. የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት
ግልፅና ተናባቢ ዕቅድ ማውጣት፣
በዕቅዱ ላይ መግባባት ላይ መድረስ፣
የግምገማና የሪፖርት ሥርዓት መዘርጋትና መተግበር፣
ሥራዎችን በመከፋፈልና በተዋቀሩት ኮሚቴዎች በጥብቅ
ዲስፕሊን እንዲመራ ማድረግ፡፡
- 19. የድርጊት መርሃ ግብር
ተ.ቁ የሚከናወኑ ተግባራት የሚከናወንበት ጊዜ ፈፃሚ አካል (ተቋም) አስፈፃሚ አካል ምርመራ
1.
ዕቅድ ማዘጋጀት
18/12/2015 ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ
ፐብሊክ ሰርቪስ
ቢሮ
2.
ኦረንቴሽን መስጠት 19/12/2015 ›› ››
3.
የሚከናወኑ ተግባራትን ለተቋማት ለይቶ መስጠት፣
19/12/2015 ›› ››
4.
የተለዩ ተቋማት ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ዕቅድ
በማውጣት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መሥራት፣ ከ19-29/12/2015 ተቋማት ተቋማት
5.
ለፕሮግራሙ የሚያስፈልጉ ልዩ ልዩ ግብዓቶችን ማሟላት፣
19/12/2015 እስከ
30/13/2015
››
6.
ለዕለቱ የሚሆኑ አጫጭር መልዕክቶች ቀረፃ ማካሄድ፣
26/12/2015
ፐብሊክ ሰርቪስ
ቢሮ
ፐብሊክ ሰርቪስ
7.
ለስልጠና እና ውይይት የሚሆን አጭር ሠነድ (ፅሁፍ) ማዘጋጀት፣
እስከ 29/12/2015 ›› ››
8.
ከሠራተኞች ጋር ስልጠና እና ውይይት ማድረግ፣
26/12/2014 ተቋማት ››
9.
በዕለቱ መከናወን የሚገባቸው ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች በከተማ፣
በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ደረጃ እንዲከናወኑ ማድረግ፣ 01/13/2015 ›› ››
10.
የከተማ ሴክተሮች በዕለቱ የተሰጣቸውን ተልዕኮ እንዲፈፅሙ
ማድረግ፣
01/13/2015 ›› ››
11.
የአፈፃፀም ሪፖርት መላክ 02/13/2015 ›› ››
- 20. ጳጉሜ 1 የአገልግሎት ቀን!
•አገልጋይነት የህሊና እርካታ ፤የስብዕና አክሊል ነው!
• በታማኝነት አገለግላለሁ፤ አደራዬን እወጣለሁ!
• አገልጋይነት ክብርም፤ታላቅነትም ነው!!
• ዝቅ ብለን አገልግለን ፤ታላቅ ሃገር እንገነባለን!
• አገልጋይነት እውነተኛ ጀግንነት ነው!
• ሀገሬን መቼም፣ የትም በምንም ሁኔታ አገለግላለሁ!
• አገልግሎት ቦታና ሁኔታ አይመርጥም!