SlideShare a Scribd company logo
1 of 20
Download to read offline
Samuel Lakew 1
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
Tribal Obsessions and Ethnic Divisions Might
Lead Ethiopia To Cognitive Impairment
ቅጥ ያጣው ጎሰኝነትና የዘር ክፍፍል ኢትዮጵያን ወደ
ባሰ የአእምሮ ቀውስና የግንዛቤ እጦት ሊመራት ይችላል
Samuel Tesema Lakew፡ (samuel.tesema@yahoo.com)
University of Nottingham, United Kingdom, 5 January 2021
Websites and Social Links:
Research Gate: https://www.researchgate.net/profile/Samuel_Lakew
ORCID iD: https://orcid.org/0000-0001-7272-1470
Web of Science Researcher ID: P-2531-2017
መግቢያ
ጥያቄ እንጠይቅ፤ ተገቢውን እና ትክክለኛውን ጥያቄ። ለጊዜው ማድረግ የምንችለው፤ ግን ደግሞ ሁልጊዜም
ማድረግ የሚገባን ይህንኑ ነው። ተገቢውን ጥያቄ ሳያቋርጡ መጠየቅ። ለምሳሌ፣ ኢትዮጵያ ሃገራችን ለምን
ከአለማችን ድሃ አገራት ተርታ ተሰለፈች? ለምን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ካላደጉና ካልሰለጠኑ ቀዳሚዎቹ
የአለማችን አገራት ጎራ ተገኘች? ለምን “ዜጎቿ” ለጋራ ጥቅም፣ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ እድገትና ብልጽግና
መተባበር፣ መደማመጥና መግባባት የተሳነን የጥንታውያኑን የባቢሎንን ሰዎች አይነት ሆነን ተገኘን? ለምን
ተፈጥሯዊ የሆነውን ክፉና ደጉን እንኳን መለየት ተሳነን? ዘርና ጎሳን መሰረት ያደረገውን የፖለቲካ ስርአት እንዴት
ልንቀበል ቻልን? መሪዎቻችን ለምን አርቆ ማየት ተሳናቸው? የእኛስ እንደማህበረሰብ ከመጣው ገዢ ሁሉ ጋር
በፍቅር የመክነፋችንንስ ነገር ምን እንበለው ይሆን?...ጥያቄው ይቀጥላል። ችግር የትዬለሌ በሆነበት ቦታና ሀገር
ጥያቄውም የትየለሌ ቢሆን አይገርምም። ለመፍትሄ ፈላጊውና ነገር ግድ ለሚለው ለሃገር ተቆርቋሪው ለምን እና
እንዴት ብሎ መጠየቁ ወደ መፍትሄው የሚያንደረድረው ድልድይ ሆኖ ያገለግለዋልና አብዝቶ ይጠይቅ። እኔም
የዚህ ፅሁፍ ፀሃፊ፤ በሀገር ደረጃ እጅግ አሳሳቢ፣ ቀንደኛና ዋነኛ ተግዳሮት ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን መሰረታዊ
ችግሮች ልናውቃቸው ይገባሉ ስል በበዕሬ ልከትባቸው ወሰንኩ። ሀገራችን አሁን ላለችበት የጨለማ ዘመን
ውድቀት፣ የማህበረሰባችን የሞራል ልዕልናው መኮላሸትና መላሸቅ መንስኤው ምን እንደሆነ በቅደም ተከተል
እያነሳሁ በማስረጃ እሞግታለሁ፤ እተቻለሁ። መፍትሄ የምለውንም እንደ አስፈላጊነቱ እጠቁማለሁ።
ችግሮቻችንን የማለባበስና ሸፋፍኖ የማለፍ ልማድ ያለን ህዝቦች በመሆናችን እንደዚህ ላሉ ዝነኛ ላልሆኑ፤
ላልተለመዱና አከራካሪ (controversial) ለሆኑ ፅሁፎች ትኩረት ባንሰጥም፤ የማንሸራሽረው ዋናው ሃሳብ ግን
የወደፊት እንደሃገርም ሆነ እንደግለሰብ የመቀጠል እድላችንን የሚወስን ብርቱ ጉዳይ በመሆኑ በእርጋታና
በስክነት በማስተዋልም ጭምር እንዲነበብ ሲል ጸሃፊው በብዙ አክብሮት ከወዲሁ አንባቢያንን ያሳስባል።
0100010111
Samuel Lakew 2
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
የድሮው እንዲህ ነበር
አንዳንድ ጠቃሚ እውቀቶቻችን እና ልምዶቻችን ከአእምሯችን ጓዳ ተደብቀው ይኖራሉ። ብዙዎች ማሰብም ሆነ
ማየት የማይፈልጓቸው የገሃዱ አለም እውነታዎች በመራራ ሃቅነታቸው ምክንያት ከሚከሰተው የስሜት ህመም
ለመሸሽ እውነትን በመቃብር ቆልፈንባት እንኖራለን። እንደምናውቀው አባቶቻችን ብልሆች፣ ጥበበኞችና ጀግኖች
እንደነበሩ የታሪክ መዛግብት ህያው ምስክሮችን አቁሞ ዛሬም ይነግረናል። የመሪነት ብቃታቸውም ሆነ ወኔያቸው
ዛሬም ይደነቃል፤ ይዘከራል። መምራትና አገር ማስተባበር የተካኑበት ጥበባቸው ለመሆኑ ከእኛም አልፎ አለምም
ጭምር ሳያቅማማ ይመሰክርላቸዋል።
አለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ፤ የሰው ልጅም ይህቺን ምድር ከረገጠባት ቀን አንስቶ በግዛትና ድንበር ምክንያት፤
እንዲሁም በሌሎች ሰዋዊና ማህበረሰባዊ የፍላጎት ሽኩቻ መንስኤ እርስ በእርሱ ሲጋጭ ቆይቷል። የሰው ልጅ
በህይወት ለመኖር በሚያደርገው ውጣውረድና ትንቅንቅ በዚህ መስመር ማለፉ ዛሬ ላገኘው የመኖር ህልውና ይህንን
ማድረጉ ተገቢም የተለመደም ክስተት ነበር፤ አሁንም ድረስ። የቅርቦቹን የጣሊያንን 2 ወረራዎችን ግጭት
ባንላቸውም እናስታውስና፤ ከነበረው የስልጣኔ ልዩነት፣የትጥቅ ዝግጅት አኳያ እንዴት የጣሊያንን ፋሺስታዊ ወራሪ
ሃይል ልናሸንፍ ቻልን ብለን እራሳችንን ብንጠይቀው የምናገኘው ትርጉም ሰጪ የሆነ መልስ የጦር ትጥቅ ወይንም
የተዋጊ ብዛት ሳይሆን አባቶቻችን ጥበበኞች ስለነበሩ ነው የሚል ይሆናል። ‘አባቶቻችን ብልህ ነበሩ’ ብዬ ስል
የእውነትም እውቀትና ጥበብ የተሞሉ ነበሩ፤ ከፍተኛ የማገናዘብና ችሎታና ችግርንም በፍጥነት የመፍታት ተሰጥዖ
የነበራቸው፤ የተጠቁና የተወረሩ ሆነው እያሉ እንኳን ሁኔታዎችን በመቀየር እራሳቸውንም ጭምር መስዋዕት እያደረጉ
ኢትዮጵያን የታደጉ የአገር ኩራት የሆኑ ብልህ መሪዎች ነበሩ። አለም ከጻፈላቸው ታሪክ የምናነባቸው ገድሎቻቸው
ይህንኑ ይናገራሉ፤ ይህንኑ ያሳያሉ [1]። የዚያ ዘመን በህይወትና ሞት መሃል ያለ ፍትግያ እና ግብግብ ቀላል ባለመሆኑ
ስህተት ሰሪው ለርስህተቱ በነብሱ ዋጋ የሚከፍልበትና ሀገሩንም የሚያጣበት ከባድ ዘመን ነበር። ውድ አንባቢያን፤
እዚህ ጋር አስተውሉ። እነዚህ መሪዎች አባቶቻችን ቀልድና ፌዝ አያውቁም ነበር። የሚሰሩት ማንኛውም ጥቂት
ምስል፡ አፄ ሚኒሊክ የመጀመሪያውን መኪና 1907 ዓ/ም ሲቀበሉና ለመንዳት ስልጠና ሲጀምሩ [2]
የምትባል ስህተት እንዳልኩት መጨረሻ ወጤቷ ከሞት የከፋም እንደሆነ ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። ሰው ሲሾሙና ወደ
ሃላፊነት ቦታ ሲያመጡት ዝምድናውን አይተው አልነበረም፤ ከሆነም ብቃቱና ንቃቱም አብሮ ታይቶ፤ ለቦታው
መመጠኑ ታሳቢ ሆኖ እንጂ። እንደዘመኑ ስልጣኔ መጠን ሙያተኞች፤ ነቃ ያሉ ቀልጣፎችና አሳቢዎች የተሻለ ቦታ
Samuel Lakew 3
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ነበራቸው። ሁሉም እንደ ችሎታው፤ እንደማሰብ አቅሙ፣ ሙያውና ቅልጥፍናው ይሾማል፤ይሻራል። በወታደራዊ
ሙያም ቢሆን ተቀጣሪው ብልህና ጤነኛ፤ ቀልጣፋ፣ እንዲሁም ጀግና፤ አገሩን እና ወገኑን የሚወድ መሆኑ ታይቶ
ሊያገለግል ይቀጠር ነበር። ምናልባት ለዛም ይመስላል በዛ ዘመን፤ የቅኝ ወራሪዎች አፍሪቃን እንደቅርጫት ስጋ
በተቀራመቷት ዘመን፤ ወታደር መሆን የተከበረ ስራ ተደርጎ በማህበረሰቡ ይቆጠር የነበረው። እነዚያ አይበገሬ የነበሩ፤
የአፍሪቃም ጭምር ኩራት የነበሩ መሪዎች አገር እንዲያድግ ህዝብም ስልጡን እንዲሆን በአቅማቸው ጥረዋል። የአጼ
ሚኒሊክ ስልክና መኪና ለመጀመሪያ ጊዜ ማስገባት፤ ከቴክኖሎጂ ጋርም ማስተዋወቅ፤ የአጼ ቴዎድሮስም መድፍ
ለመስራት ያደረጉት ጥረትና እውን ለማድረግም የሄዱበት እርቀት ሁሉ ይህን ለስልጣኔ የነበራቸውን ጉጉትና
ፍላጎታቸውን አመላካች ነገሮች ናቸው [3]። ስልጣኔን መቀበልና መዘመን አገርን ከጠላት ለመጠበቅ ብርቱ መንገድ
መሆኑን የተረዱ ነበሩ። በንጉሱ ጊዜም ቢሆን በርካታ የጭቆናና ብዝበዛ እንዲሁም ሌሎችም ችግሮች ተንሰራፍተው
የነበሩ ቢሆንም፤ ማህበረሰቡ ለዘመናዊ ትምህርት ተነሳሽ እንዲሆን በጥቂቱም ቢሆን ይበረታታ ነበር። አልፎ አልፎም
ከሲቪሉም ይሁን ከሚሊተሪው ዜጎች ተምረው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ በማለት በዘመኑ ሰለጠኑ ወደሚባሉት
የምዕራቡ አለም እውቀት ቀስመው እንዲመለሱ ይደረግ እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ያወሳናል። የቀደሙትን
የኢትዮጵያ ሃገራችን መሪዎች ትልቁ ጠንካራ ጎናቸው የሃገር ወዳድነታቸውና ለጠላት ያለመንበርከክ
እንቢተኝነታቸው ነበር። ይህም የተለየና በአለም ያልታየ ወኔ እና ጀኝነት፣ እኛ ኢትዮጵያውያንን ብቸኛ በቅኝ ግዛት
ያልተገዛን እና ያልተደፈርን እንድንሆን አድርጎናል። በዚህም ምክንያት በዘመናችን ሁሉ ጠንካራ ኢትዮጵያዊ ስሜት
ያለው፤ ከሀገሩም አልፎ ለአፍሪካም ኩራት የነበረ የሃገር መከላከያ መገንባት ችለን እንደነበረ ታሪክ ያመላክታል።
ዲሞክራሲና ዘር ተኮር ፖለቲካ
“Democracy is the worst form of government – except for all the others that
have been tried.” [Winston Churchill]
አሁን ደሞ ጊዜያትን እና ሃሳቦችን ቦታና ጊዜ መድበን እንያቸው። አገራችን ኢትዮጵያ እንደ ሃገር መቆየትና መኖር
መቻል ካለባት ወይንም እኛ ዜጎች መኖር አለብን ብለን ካመንን፤ እንደ ቀደሙት ጊዜያት ሁሉ ዘመኑ በሚፈቅደውን
የአስተዳደር ስርአት ሳይሆን ለዘመኑ የሚመጥነውን መልካም የፖለቲካ ስርአት መገንባት ይገባናል ብዬ አምናለው።
ይህም የሃገርን ታሪክ የሚያውቁና የሚያከብሩ፤ የማህበረሰቡን ባህልና እሴት ጠንቅቀው የተረዱ አዋቂዎችና ብልሆች
የመሪነቱን ቦታ በየመስኩ በተዋረድ ሊይዙት፤ ሊመሩትና ሊያስተዳድሩት ይገባል ብዬ አጥብቄ እሞግታለሁ። ይህም
ሃቅ ችግሮች ሳይከሰቱ ገና በግዜ ቢገባንና ብንተገብራቸው መልካም ነበር። አለዚያ ግን አንድ ቀን በባትሪም ፈልገንና
ለምነን የማናገኛቸው የምጥ ጊዜያት መድረሱ አይቀርም። ዘር፣ ጎሳ፣ ብሄር፣ ቀለም እና ቋንቋ የምንላቸው ነገሮች ሁሉ
ቦታ ሳይኖራቸው፤ ማሰብና ማገናዘብ የሚችሉ፤ በትምህርትም ብቃት የተደገፉ ሰዎችን በሁሉም የስራና የትምህርት
መስክ ለራሳችንና የልጅ ልጆቻችን የወደፊት የመኖር ህልውና እንዲሁም ሁለገብ የሃገር ደህንነት ስንል እንደ
ስልጡኖቹ ሀገራት ሁሉ እኛም ወደ መሪነት ሚና እንዲህ ያሉትን ልናመጣ ይገባል። በሃገራችን ሰዎች ችሎታቸው
በሚመጥናቸው የስራ መስክ እና ደረጃ ላይ ሲያገለግሉ አይታዩም። ይህም መመዘኛው ዘርና ጎሳዊ ፖለቲካ በመሆኑ
ነው። በአንድ ክልል ውስጥ ካለ አንድ ከክልሉ ከሚኖር የህክምና ዶክተር ይልቅ አንድ ልምድ የሌለው የግል ኮሌጅ
ውስጥ ተየሰለጠነ የክልሉ ነዋሪ የነርስ ሙያ ምሩቅ ለቅጥር ተመራጭ መሆኑ አያጠያይቅም። በዚህም ሳቢያ ታሞ
የሚድን አይኖርም። ወደ ክሊኒኩ የሚገባ እንጂ የሚወጣ ህይወት አይኖርም። የዘር ፖለቲካ መሠረቱ ደም ነው።
ለሰው ልጅ ህይወት ክብር የለውም። ህይወትና እውቀት ግን አይነጣጠሉም። እውቀት ያለው፣ ጥበብንም የማይንቅ
ውጣ ውረድን ተቋቁሞ በህይወት ይኖራል። እኔም የዘር ፖለቲካን የእውቀትና ጥበብ ጠላት ነው እለዋለሁ። ይህም
እውቀትንና ጥበብን የመጥላት ልዩ ባህሪው ክቡር ለሆነውን የሰው ልጅ ቀንደኛ ጠላት እንዲሆን አድርጎታል። የዘር
Samuel Lakew 4
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ፖለቲካ ልክ እንደ ቫይረስ ሁሉ ለቀጣይ ህልውናው የሚኖርበትና የሚባዛበት በህይወት ያለው አካል (host)
ያስፈልገዋል። ይህም ሲሆን ብቻ እንደቫይረስ በፍጥነት ለመዛመት ይችላል። የሰውን ልጅም እንደ ሰው እንዲያስብ
የተፈጠረለትን አእምሮ በቁጥጥር ስር በማዋልና በመቆጣጠር ከእንሰሶች በታች እንዲያስብና እንዲኖር ያስገድደዋል።
በዚህም ምክንያት የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ተግባራቸውና ንግግራቸው አብሮ አይሄድም። የላሸቀ የሞራል
ልዕልናቸውና የዘቀጠው ስብዕናቸው ለዚህ ጥሩ ማሳያ ሊሆን ይችላል። ሰው ምን ይለኛል ብሎ የሚወቅስ ህሊና
የላቸውም። ማታለልና ማምታታት የዚህ አይነት ዘረኛ አገዛዝ ዋነኛ ስልት ነው። ሁሉም ሰው ለነሱ እቃቃ መጫወቻ
ተሰርቶ የተሰጣቸው ስለሚመስላቸው፣ ህሊና ቢስ መሆናቸውን ላልተረዳ የዋህ ግለሰብ ለሰው ልጅ ያላቸው ጭካኔ
እና ደመ ቀዝቃዛነት ቢመለከትም ምንጩ ምን እንደሆነ ግን አይገባውም። ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ በዘሩና በጎሳው
እንዲሁም በቋንቋው ከፋፍሎ ለመመደብ፤ እንደ እንሰሳም ፓርክም አይነት አድርጎ በክልል ሸንሽኖ በማጎር፤ ከዚያም
መልሶ ደሞ እስከፈለጉ ጊዜ ድረስ ብቻ የኢትዮጵያ አካል እንዲሆኑ ህግ በመደንገግ ለማታለል ወዘተ ድረስ መሄዱ
... ለዚህ የክፋት ስራ አመንጪና ፈጣሪነት ለመብቃት አንድ ሰው ምን ያህል ጥልቅ የሆነ ጨለምተኝነትና የአእምሮ
መዛባት ቢከሰትበት ይሆን የዚህ ሰይጣናዊ የፈጠራ ባለቤት መሆን የቻለው በማለት በማዘንም ጭምር አስባለው።
እንዲህ ስል እራሴን ጠየኩ፤ እኛ ኢትዮጵያውያን ምን አይነት ፍጹማዊ አስተዳደራዊ ስርአት ይሆን የምንፈልገው?
የዲሞክራሲ አስተዳደር ስርአት ይሆን ወይስ እንደዚህ በዘር እና በመብት ነፃነት እያሳበበ ቀጥቅጦ የሚገዛ የዘር
ፖለቲካ? ዲሞክራሲስ ቢሆን? ማነው ዲሞክራሲ ፍጹማዊ መንግስተ-ሰማይ መሰል ስርአትን (Utopia) ያመጣል
ያለው? እንደ እኔ ዲሞክራሲ የሰው ልጆችን ደህንነት ዋስትና የሚያረጋግጥ መልካም የአገዛዝ ስርአት ነው ብዬ
አላስብም። መራጮቹ መልካም ስብእና ካላቸውና የሚመርጡትን ሰው ጠንቅቀው ካወቁ፤ ምናልባት ዲሞክራሲ
እዚህ ጋር ይሰራ ይሆናል። ምክንያቴንም እነሆኝ። ዲሞክራሲ ብዙሀኑ ትክክል ነው ብሎ የሚያምን እና
ለድምጻቸውም ዋጋ የሚሰጥ ስርአት መሆኑን አውቃለሁ። ብዙሃኑ (majority) ትክክል ነው ብሎ በሚያምን
አስተሳሰብ ላይ በመገንባቱም ብዙዎቻችን ለዲሞክራሲ ያለን አዎንታዊ ዝንባሌ ከዚሁ የተቀዳ ለመሆኑ
አያከራክርም። ታሪክ ግን የሚነግረን ይህ እውነት አለመሆኑን ቢሆንስ እንቀበልና እራሳችንን እናስተካክል ይሆን?
ብዙሃኑ ሂትለርን መርጦ አብሮት ብዙ ርቀት ተጉዟል። ላመኑበትም ሃሳብ የ 6 ሚሊዮኖችን የአይሁዶች ህይወት
ለሂትለር ደስታ ቀጥፈው እንደ መስዋእት በደስታ አቅርበውለታል። የምለው ነገር ብዙሃኑ ሁሌም ትክክል
የማይሆንበት አጋጣሚ በመኖሩ ዲሞክራሲም እዚህ ጋር ይወድቃል ባይ ነኝ።
የፍልስፍናውም ሆነ የዲሞክራሲው አመንጪና ፈጣሪዎች ጥንታውያን ግሪኮች ሆነው ሳለ ፍልስፍናው
ዲሞክራሲውን መቃወሙን መዘንጋት የለብንም። ለሃሳቤ መጎልበት የሶቅራጥስን ሙግት ልግዛውና ዲሞክራሲ
ለብዙሃኑ ድምጹ እንዲሰማለት ስለሚያደርግ ብዙሃኑ ህዝብ በምርጫ ወቅት የሚወዳደረውን እጩ የህክምና ዶክተር
ወይስ አፈ ቀላጤውን የጣፋጭ ምግብ ነጋዴ ይመርጣል? ምግብ ሻጩ ሰው በምግቡ ጥፍጥናውና በህዝቡ
መሃይምነት ተጠቅሞ በማታለል ይመረጣል። ህዝቡም እውቀት አልባውን ምግብ ሻጭ መሪያቸው አደረጉ ማለት
ነው። በዚህ ውስጥ ግን ጉዳቱን የሚያውቁት ጥቂቶች ናቸው። እናም ሶቅራጠስ ይህ ትክክል አይደለም ይለናል።
የመራጭነት እድል ለማግኘት ሰዎች ምን እንደሚመርጡ፤ ተያያዥ ጥቅምና ጉዳቱንም አጥንተው ሲረዱ ነው ጥሩ
መራጭ የሚሆኑት። መራጭነት የዜግነት ስጦታ ብቻ መሆን የለበትም። መራጩ ብዙሃን መሃይምና በቀላሉ
የሚታለል በሆነበት የእኛ አይነት ማህበረሰብ ውስጥ ዲሞክራሲ ማለት የህጻን ልጅ ጨዋታ አይነት ነው። እንዲህ
እንደ ጥንቷ ግሪክ ያለ ማህበረሰብ ክፉና ደጉን የሚለዩት ወይም እንበልና ወደ እውነተኛው ያልተጭበረበረ
ዲሞክራሲ የሚመለሱት ለህይወት አስጊ የሆነ አደጋ ወይም ክስተት ሲመጣባቸው ብቻ የመሆኑ ክስተት ነገሩን ትንሽ
Samuel Lakew 5
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
አስቂኝም ቢጤ ያደርገዋል። ለምሳሌ እንበና የመርከብ ጉዞ ስታደርግ በመርከቡ ያኩ ሰዎችን ሰብስባቸውና ለመርከቡ
በትክክል መስራት እንዲረዳ ሰዎችን ምረጡ ብትላቸው ሙሉ በሙሉ የመርከብ ትምህርትና ልምድ ያለውን ብቻ
ይመርጣሉ። ለምን? እዚህ ጋር የህይወት ጉዳይ በመሆኑ አይቀለድምና ችሎታና ብቃት ካላቸው ውጪ ምረጡም
ተብለው ቢመከሩም ቢዘከሩም ፍንክች አያደርጉትም። ዲሞክራሲ ሁሌም እንዲህ ቢሆን እውቁ የግሪክ ፈላስፋም
ሆነ ከዘመናት በኋላ እውነት እንደሆነ የተረዳሁት እኔም ዛሬ በደገፍነው ነበር። ታዲያ ይህን እውነታ ወስዶ በአገራችን
ካለው ነገር ጋር አስተያይቶ ሁኔታውን ላጤነው የቅርቡቹ ሁለት ጦርነቶች ጥሩ ማሳያ ናቸው። በነዚህ ጦርነቶች
ምክንያት የተባረሩ ፓይለቶችና እውቅ የጦር ጀነራሎች ተለምነው ወደ ስራቸው ሲመለሱ አይተናል። ታዲያ ለምን
እውቀት አልባዎች እንዲመሩንና ለህይወትና ለወንበራቸው አስጊ እስኪመስላቸው ድረስ በመሃይምነታቸው እውርነት
ሊያጠፉን እስኪደርሱ ድረስ ፈቀንላቸው? ለምን ታዲያ ለህይወታችን ዋጋ ከሰጠን መርከቧ በማእበል ወቅት ሆነ
ያለ ማእበል በባለሙያዎች እንድትነዳ አናደርግም?
ዲሞክራሲ በሁለት ምክንያቶች ውድቅ ሊሆን ወይም ላይሰራ ይችላል። አንደኛው በብዙሃኑ አማካኝ የግንዛቤ
ብቃትና የእውቀት ልክ ሲወሰን ሌላው ደሞ የተመራጩ ግለሰብ ማንነትና ስብእና ላይ ይሆናል። የብዙሃኑ ውሳኔ
እና የምርጫቸው ውጤት ምንነት እንዲሁ እንደ ብዙሃኑ ማንነት፣ ባህል፣ እምነት፣ የስልጣኔ መጠን ወዘተ ይወሰናል
ማለት ነው። አንዳንዴ እነዚህ ‘ብዙሀን’ (majority) ተብለው የሚጠሩት የማህበረሰብ ክፍሎች ልክ በ 1930ዎቹና
40ዎቹ እንደነበሩት ብዝሀው የጀርመን ህዝብ እርኩስ ሃሳብ አንግበው ቢነሱስ? ለአናሳዎችስ ይህ ማለት እንደ
አይሁዶች ይጨፍጨፉ ብሎ የይለፍ ፈቃድ እንደመስጠት አይሆንም? በሌላ መልኩ ደግሞ እንበልና ብዙሀኑ ህዝብ
መሃይምና አማካኝ ዝቅተኛ የግንዛቤ ክህሎት (በተቀራራቢ ትርጉም ዝቅ ያለ IQ1 ያላቸው ሰዎች ለማለት ነው)
ቢኖራቸው፤ እንዴት አውቀውና አገናዝበው ሀገር የመምራት ብቃት ያለውን፤ የማሰብና ማስተዋል ችሎታ፤ ሙያና
ስብዕና ያለውን ተፈጥሯዊ መሪ አስተውለውና መርምርው መምረጥ ይችላሉ? ይህንንስ ጥያቄ የዲሞክራሲ መርህ
ይመልሰዋል ወይ? በዚህ አጋጣሚ አንድ ነገር ለአንባቢዎቼ ከወዲሁ በጊዜ ግልጽ እንዲሆን ያህል፤ ለአሻሚና
አላስፈላጊ ትርጉሞች አንባቢን እንዳይጋብዝ በማለት እንዲሁም የዚህ ጽሁፍም አንዱና ዋነኛ ማጠንጠኛ ሃሳብ
በመሆኑ ይህ IQ1
ብለን ከምንለው ሃሳብ ጋር የተያያዘውን ነገር አጥርቼው ባልፍ ተገቢ ይሆናል ብዬ አስባለው።
እንደሚታወቀው የማሰብ ችሎታና IQ ብለን ከምንጠራው የዚሁ መለኪያ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ንግግሮችና
ውይይቶች ብዙ ሰዎች እንደማይወዱትና ምቾት እንደማይሰማቸው በሰፊው ይታወቃል። ቢሆንም እውነት ሲነገር
የሚወራው ተቀናንሶና ተጨማምሮ ባለመሆኑ፤ እኔም ከእነዚህ የማህበረሰብ እምነቶችና ከስነልቦናዊ ተጽዕኗቸው ነጻ
በመሆን እውነትን እንደሚፈል ሰው ይህንኑ እጽፋለው። እውነትን ለማግኘት በምናደርገው ጉዞ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ
በዚሁ በ IQ ዙርያ ልንወያይና ልንጽፍም ይገባል ስል እናንተንም እመክራለሁ፤ አበረታታለሁ። የሃይማኖት ሽፋን
በማላበስና መሰል ነገሮችን በመጠቀም አላስፈላጊ ትልጓሜ ለመስጠት መሞከሩ አልያም ‘ለሃገር ክብር’ በሚል ተያያዥ
እውነታን መደበቅ የማህበረሰባችንን ችግር ከማባባስ የዘለለ ምንም ፋይዳ አይኖረውምና እኔ በነጻነት እንደምጽፍ
ሁሉ እናንተም ያለምንም ተጽዕኖ ነገር ግን በማስተዋል መወያየትና ሃሳብን ማንሸራሸሩ ክፋት የለውም ባይ ነኝ።
1
IQ ማለት Intelligence Quotient ለሚለው የእንግሊዘኛ ምህጻረ ቃል የቆመ ሲሆን፤ የፈተናውም ውጤት የአንድን ሰው ተፈጥሮሯዊ
አዕምሯዊ ችሎታና እምቅ ክህሎት ለመለካት እንደመሳሪያ የሚያገለግል ነገር ነው። የግለሰቡ ተፈጥሯዊ አስተሳሰብ ፣ አመክንዮ አሰጣጥ እና
ችግር አፈታት የመሳሰሉ የግንዛቤ ችሎታዎችን ለማንፀባረቅ ይጠቅማል።
Samuel Lakew 6
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
የሃገራችን (የኢትዮጵያ) አብዛኛው ህዝብ ወይንም ማህበረሰብ በእኔ እምነት፤ ግን ደግሞ ምክንያቱ ሙሉ በሙሉ
ባልገባኝ ሁኔታ ነገሮችን የማሰብና የማገናዘብ ብቃቱ እጅግ ዝቅ ያለ እንደሆነ ተገንዝቤያለሁ። ምንም እንኳን ይህ ጉዳይ
ወይንም ችግር በመላው የአገሪቱ ክፍል የምናየውና የምንረዳው ነገር ቢሆንም፤ ብዙዎች ጉዳዩን ማየት የምንችል
ሰዎች ግን ማመን አንፈልግም። ችግሩን እንደመመርመርና መፍትሄ ካለውም አጥንቶ መፍትሄ እንደመፈለግ፤
ምሁሮቻችን ግን እነሱም በክህደት ውስጥ ገብተው ሁሉም ሰላም እንደሆነ አድርገው ችላ ብለውታል። በቂና አሳማኝ
በሆነ መልኩ ባይሆንም የውጪ ጥናቶችም ቢሆኑ ይህን ሃሳብ ከአንዴም ሁለቴ በማረጋገጣቸውና የኢትዮጵያን
አማካኝ IQ መጠን በቁጥር 63 እና 67 በማለት ከሌሎች የአለም አገራት ዝርዝር ውጤት ውስጥ አካተው መጻፋቸው
ብዙ ቁጣ ቀስቅሶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው። ነገር ግን ትዕግስት አግኝቶ ነገሩን ላስተዋለው ሰው የነበረው
ሁሉ ቁጣና ስድብ፤ ምክንያታዊነት የጎደለው ክርክርና ማብራሪያዎቹ በራሳቸው የኢንተርኔት መረጃው መሰብሰብና
ማየት ለቻለ ሰው አንዱ የውጤቱን ትክክለኛነት ወይም ተቀራራቢነት ማሳያ ሆኖ ያገለግለዋል ብዬ አምናለው።
በግልጽ ለመናገር ያህል፤ ህዝባችን ለማሰብ፤ ለማገናዘብና ነገሮችን ለመመርመር የሚደክመውና የሚዝል ህዝብ ነው
ብዬ ብል ማጋነን አይሆንብኝም። እጅግ ብዙ የሚባለው የኢትዮጵያ ህዝብ ከእቅድ ይልቅ በደመነብስ መመራትን፤
ያለምክንያት መወሰንና መተግበርን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ነው። ከዚሁ ማህበረሰብ የወጡ መሪዎችም ያለምክንያት
እረግጠውና ጨቁነው ሲመሩት ሰጥ ለበጥ ብሎ ይገዛል። ሲገድሉትም በዝምታ ይገደላል። ይህም በሌሎች ሰዎች
‘ትዕግስትና ቻይነት’ እየተባለ የማሳሳቻ ታርጋ ይለጠፍበታል። እውነታው ግን ያለማጋነን ለዚህ ህዝብ መንግስት
ማለት ትርጓሜው አምላክ እንደማለት ያለ ነው። ‘በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ’ እንዲሉ፤ ከዝቅተኛ ንቃተህሊናና
የማገናዘብ ችሎታ ላይ መሃይምነት ተጨምሮበት፤ አሁን አገራችን ያለችበትን አጣብቂኝ ሁኔታ ስናስበው ውጤቱ
ምን ሊሆን እንደሚችል መገመቱ ብዙ ምርምር የሚጠይቀን ጉዳይ አይሆንም። የማህበረሰባችን ‘ዲሞክራሲያዊ
ስራትን’ አስፋኝ ይሆናል የተባለው ብዙሃን (majority) ምድቡ የትኛው ጋር ነው? ያልተማረውና በደመነብስ
የሰማውን ሁሉ አምኖ በግምት የሚመርጠውን ወይስ እንደ የአዶልፍ ሂትለር ጀርመን ክፉ ሃስብ ተጠናውቶት
በወደፊቷ ኢትዮጵያ የምናባዊ ስዕሉ ወስጥ ከአንድ ብሄር በስተቀር የሌላውን ኢትዮጵያዊ መኖር የማይታየው
(tyranny of the majority2
)? ወይስ ሁለቱም?
Professor Jordan Peterson
“የማህበረሰብ ህልውና በሴቶች እጅ ነው”
ከሁለት አመታት በፊት የአለማችን ምርጥ የስነ ልቦና ተመራማሪ በሆነው እውቁ በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር
ጆርዳን ፒተርሰን የሚተላለፍ ፐብሊክ ሌክቸር ላይ አንድ እንዳስብበት ያደረገኝን አከራካሪ ሃሳብ ሲናገር አዳመጥኩ።
ነገሩ ባጭሩ እንዲህ ነው። አንድ ወጣት ሰው ፖስታ ውስጥ ወረቀቶችን በልኩ አጣጥፎ ለማስገባት ሲታገል ይህ
ፕሮፌሰር ይመለከተዋል። 30 ደቂቃ አለፈ፣ ወጣቱ ሰው ግን አስተካክሎና አጣጥፎ ማስገባት አልቻለም። በኋላም
ሊረዳው በመወሰን የተለያዩ ወረቀቶችና ፎቶዎች እንዴት ፎቶው ሳይታጠፍ ማስገባት እንደሚችል 30 ሰአታት የፈጀ
ስልጠና ሰጠው። ይህን ሰው አዲስ ሙያ ማስተማር ከባድ ነበር። ሌላ አንድ ተራ ነገር ለመማርም እንዲሁ 6 ወርና
አመት ይፈጂበታል እንደማለት ነው። ይህን ሰው ስራ የሚቀጥረው የለም። የነጻ አገልግሎት በመስጠት
(volunteering) ነበር የሚያገለግለው። በኋላ ግን እሱንም ቢሆን ሊቀጥል አልቻለም። የሚያደርገው መስራት
2
Tyranny of The Majority (Tyranny of The Masses) is an inherent weakness to majority rule in which the
majority of an electorate pursues exclusively its own objectives at the expense of those of the minority
factions. This results in oppression of minority groups comparable to that of a tyrant or despot. [17]
Samuel Lakew 7
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ሳይሆን እንዴት እንደሚሰራ ሰዎችን እርዳታ በመጠየቅ የስራውን ክፍለ ጊዜ ማቃጠል ነበር። በኋላም ቀጣሪዎቹ
የሰለቻቸው ይመስላል ከነጻ አገልግሎት ስራውም አባረሩት። ፕሮፌሰር ፒተርሰን እንዳለው ይህ ሰው በጣም ዝቅተኛ
(ከ 80 በታች IQ) እንዳለውና፤ ነገር ግን ከውጪው ሲታይ እንደማንኛውም ጤነኛ ሰው እንደሆነና ላዩን አይቶ
የዚህን ሰው ችግርና ሁኔታውን ለመገመትም እንደሚከብድ ገልጿል [4]።
ፕሮፌሰር ፒተርሰንን እንደሌሎች በዘርፉ እንደተሰማሩ ተራ የስነልቦና ምሁራን አድርጌ አላየውም። ምንም እንኳን
ሁሉንም አመለካከቱን እና ስራዎቹን እጋራለው ባልልም፤ እጅግ ምጡቅ ተመራማሪና መምህር በመሆኑ አድናቂው
እንድሆን አድርጎኛል። እውነታን አጣቅሶ በማስረጃ አዋዝቶ ነብስ ዘርቶበት የሚሞግተውን ሃሳብ የሚያቀርብ፤ ለሰው
ልጆች ጠቃሚ የሆነ ጥሩ ችግር ፈቺ ተመራማሪና መምህርም ነው። በአለም ላይ ልናገኛቸው ከምንችላቸው ጥቂት
የዘርፉ ምሁራን ውስጥ አንዱና ቀዳሚው ሰው ነው ብልም ማጋነን አይሆንም። ይህን የምለው የዚህን ግለሰብ ለሰው
ልጅ ያለውን ጥቅምና ዋጋ ግምት ውስጥ በመክተት ነው። ፕሮፌሰሩ በዚህ ሌክቸር ወቅት ታዲያ ትኩረት ሰጥቶ
በዋናነት ይናገር የነበረው የማህበረሰቡ ግማሽ አካል ስለሆኑ የሴቶች እህቶቻችንን ባህሪ ሲሆን፤ ይህም እንዴት አድርጎ
ማህበረሰብን እየቀረጸና አየመራ እንዳለ፤ እንደነበረም የሚያብራራ ነበር። ለመሆኑ ሴቶች አብሮ መኖርን ሲያስቡ
ምን አይነት ወንድን ነው የሚያስቡት ወይም የሚማርካቸው/የሚስባቸው? ነገሩ ሰፊና ፕሮፌሰሩ የሰራውንም ምርምር
የሚያካትት በመሆኑ እኔም እዚህ ልጽፈው ቦታው ባይሆንም፤ እጅግ ጠቃሚ የሆነውን ክፍል ብቻ ለሃሳቤ
ማጠናከሪያና አስረጂ ሆኖ ስላገኘሁት በአጭሩ
ሃሳቡን ጨምቄ እንደሚከተለው ፅፌዋለሁ።
Jordan Peterson, a Canadian psychology professor (From his reddit blog)
ዘመኑ የእውቀትና የመረጃ ነው። በዚህ ዘመን በምእራቡ አለም ትንሽ የተሻለ IQ ያለው ግለሰብ ባብዛኛው ቢያንስ
የመጀመሪያ ዲግሪ ይኖረዋልና በንፅፅር ሲታይ ከሌላው የተሻለ አመታዊ ገቢና የኑሮ ደረጃ አለው። ቀጣሪ
ካምፓኒዎችም የተሻለ ልምድና የትምህርት ደረጃ ስለሚጠይቁ፤ ቃለመጠይቃቸውም ቀሪውን መልስ
ስለሚመልስላቸው፤ ዝቅተኛ IQ ያለው ሰው የተሻሉ የስራ ቦታዎችን የማግኘት እድሉ የመነመነ በመሆኑ የአቅሙን
በመፈለግ የሚመጥነው የስራ አይነት ላይ መሰማራቱ፤ ለዚያም የሚመጥን የሙያ ስልጠና ወስዶ መዘጋጀቱ
የተለመደና ማህበረሰቡም የተቀበለው ጉዳይ ነው። በሌላ አገላለጽ፤ አንድ ሰው በምዕራቡ አለም የአኗኗር ዘዬ ስኬታማ
ከሆነ የተሻለ የማሰብና የማገናዘብ ብቃት አለው፤ የተሻለ IQ አለው ወደ ሚለው ድምዳሜ ያደርሰናል። ይህን ይዘን
ወደ አፍሪቃና በተለይ ወደ ኢትዮጵያ ስንመለስ የሰዎችን የመቀጠር ሁኔታና በአጠቃላይ የስኬታቸውን መነሻ
ስንመረምር ነገሩ ፈጽሞ ሌላ ታሪክ ህኖ እናገኘዋለን። በአገራችን ለ 30 አመታት ስር ሰዶ በተንሰራፋው ዘር፣ ቋንቋ
Jordan Bernt Peterson (born 12 June 1962) is a Canadian
clinical psychologist and a professor of psychology at the
University of Toronto. He began to receive widespread
attention in the late 2010s for his views on cultural and
political issues.
Born and raised in Alberta, Peterson obtained bachelor's
degrees in political science and psychology from the
University of Alberta and a PhD in clinical psychology from
McGill University. After teaching and research at Harvard
University, he returned to Canada in 1998 to join the faculty
of psychology at the University of Toronto. In 1999, he
published his first book, Maps of Meaning: The Architecture
of Belief, which became the basis for many of his subsequent
lectures. The book combined information from psychology,
mythology, religion, literature, philosophy, and neuroscience
to analyse systems of belief and meaning.
Samuel Lakew 8
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
እና ክልል ተኮር የሆነው የሃሰት ፌዴራሊዝም (Pseudo Federalism3
) ፤ አብዛኛው አቅምን የሚጠይቁ ለሀገር
ጠቃሚ የሆኑ የስራ መደቦች ግለሰቡ በዘሩና በቋንቋው እንዲሁም ለገዥው መደብ በተግባር በሚያሳየው ታማኝነትና
ተገዥነት የሚሰጠው ስጦታና ችሮታ እንጂ ተምሮ ባገኘው እውቀትም ሆነ ልምድ አዳብሮ የተሻለ በመሆኑ ተገብቶት
የሚቀጠርበት አይደለም። ታዲያ አሁንም ወደ መዕራባውያኑ ባህል ስንመለስ አንዲትን ሴት ልጅ የሚማርካት ነገር
የሰውየው ሃብታም መሆን ሳይሆን ስኬታማና ዲሲፕሊኑ ሲሆን ይህም የተሻለና ለዚህ እንዲበቃ ያደረገው የኝዛቤ
ክህሎት ወይም IQ እንዳለው ስለሚያመለክታትና ስለሚጠቁማት ነው ብሎ ያምናል፤ ፕሮፍፌሰር ፒተርሰን።
በተቃራኒው በኛ ሀገር የተሻለ ስኬት ላይ የሚገኙ ሰዎች በሴት እህቶቻችን ብቻ ሳይሆን በማናችንም ቢሆን ቀድሞ
ወደ አእምሯችን የሚመጣው ሃሳብ የግለሰቡ የመንግስት ሰው የመሆን እድሉ ከፍተኛ መሆኑ ነው።
እንበልና ትንሽ ወደ ኋላ አንድ ሺህ አመት ያህል ተጉዘን ብንመለከት፤ የዚያ ዘመን ሴቶች የሚስባቸው ወይንም
የሚማርካቸው ወንድ ምን አይነት ነገሮችን ያሟላ ይሆን ብለን እንጠይቅ። የምናገነውም መልስ እንደዚህኛው ዘመን
ትልቅ የ IQ መጠን ያለው ሰው ሳይሆን እጅግ ትልቅ ተክለ ሰውነት ያለው እንደነበር ከአለም የታሪክ መዛግብት
እንረዳለን። የግሪኮችን አፈታሪክ እንኳን ትተን የእኛን ሃይማኖታዊ የታሪክ አዘል ማስረጃዎችን ብንወስድ እንኳን፤
በመጽሃፈ ሄኖክ [5] እና መጽሃፍ ቅዱስ [6] ፤ የሰው ልጅ ሴቶች ልጆች ከተራ ሰው ይልቅ ለየት ላሉ ሰዎች ወይም
መለኮታዊ ለመሰሏቸው ፍጡሮች የመሳብ አዝማሚያ እንደነበራቸው ሳይጠቁሙ አላለፉም። እዚህ ጋር ይህ
ተወራራሽ የሆነ የሰው ልጅ ስነልቦናዊ ተፅዕኖ በኛም አገር አብዛኞቹ እህቶቻችን ዘንድ ለጸጉረ ልውጦች፣ ለጣሊያን
ወይም ለኩባ ክልሶች እንደሚማረኩላቸው አይነት ባለ መልኩ አሁንም ድረስ እንደሚንጸባረቅ ልብ ይሏል። ታዲያ
የድሮው ዘመን ሴቶች ለምን ምርጫቸው ይህ ሆነ ለሚለው ጥያቄ ውሃ የሚያነሳልን ልናገኘው የምንችለው ሚዛን ደፊ
መልስ የዘመኑ ውድ እና ተፈላጊ ነገር ደህንነት (safety/security) ስለነበር ነው። በአጭሩ ቀጥታ ስንናገረው
አንዲት ሴት የመኖር ህልውናዋን ለማረጋገጥ ከጠላት የሚጠብቃት ጉልበተኛና ጡንቸኛ ወንድ ነበር የሚያስፈልጋት
ማለት ነው። ግዙፍ የሆነ ጡንቸኛ ሰው በዘመኑ የተሻለ የኢኮኖሚ ዋስትናም ስለሚኖረው የሴቷ እረጅም እድሜ
የመኖር እድሏ (probability of survival) ይጨምራል። ትልቅ ጡንቻ በድሮ ዘመን፤ ትልቅ አእምሮ/የማሰብ
አቅም ደግሞ በዚህ ዘመን ማለት ነው። ይህን ስል የዝግመተ ህይወት (Theory of Evolution)4
ሰባኪም ሆነ
ተቀባይ ሆኜ አይደለም። የዚሁ መስክ ተመራማሪዎች ለራሳቸው እንዲመች አድርገው በሳይንስ ስም የተረኩትን
ተረት ባልቀበልም አንዳንድ እውነት የሆኑ አሳማኝ ማስረጃ ያላቸውን፤ በዚህም ዘመን በአይን የሚታዩና የሚጨበጡ
ከላይ እንደጠቀስኩት ያሉ ጽንሰ ሃሳቦችን ግን እጋራቸዋለሁ። ለምሳሌ ያህል ከእነዚህ ውስጥ የቻርለስ ዳርዊንን
“ብቃት ያለው ይኖራል” (Survival of the Fittest) ፅንሰ ሃሳቡን ብንወስድ መሉ በሙሉ ባይሰራም፤ ሌሎችም
የሰውን የመኖር እድል የሚወስኑ ጉዳዮች ያሉ ቢሆንም፤ ከማነሳው ሃሳብ ጋር አብሮ የሚሄድ ተፅዕኖ ፈጣሪ ገዢ
3
የውሸት ፌዴራሊዝም (Pseudo Federalism) ማለት ከተለመደው ወጣ ያለና በሌላው አለም የፌዴራሊዝም ባህሪያት ያፈነገጠ፤
ለይስሙላ ብቻ በህገ መንግስት ላይ ይስፈር እንጂ የተለያዩ ክልሎች ወይንም ፓርቲዎችን በራሳቸው የመወሰን እድል የማይሰጥ፤ ነፃና
ዲሞክራሲያዊ ምርጫን ከወረቀት በቀር ይርማይተገብር፤ ከዚያም አልፎ በእኛ አገር በተለይ አንደሚታየው ለአገር ህልውናና አንድነት ፀር
የሆነ ክልሎችን እስከመንገንጠል የሚያደርስ እንደ አንቀፅ 39 አይነት ያለና ዜጎችን ከክልላቸው ውጪ የመኖር መብት የሚነፍግ እንዲሁም
ሌሎች አደገኛ የሆኑ ህግና ደምበችን የያዘ በመሆኑ ነው።
4
In the 1850s, Charles Darwin wrote an influential and controversial book called The Origin of Species. In
it, he proposed that species evolve (or, as he put it, undergo "descent with modification"), and that all living
things can trace their descent to a common ancestor. Darwin also suggested a mechanism for evolution:
natural selection, in which heritable traits that help organisms survive and reproduce become more common
in a population over time [7].
Samuel Lakew 9
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ሃሳብ ነው ብዬ ግን አምናለሁ። በድሮ ጊዜ ብቃት ማለት ትልቅ ጡንቻ ወይም ጉልበት ያለው ማለት ነበር፤ አሁን
ደሞ የአእምሮ የማሰብ ብቃት (Intelligence) ሆኖ እናገኘዋለን። ታዲያ ይህ ማለት በዚያ ዘመን የሰው ንቃተ
ህሊና ዋጋ የለውም ማለት እንዳልሆነ ይስተዋል እላለሁ። ሳልጠቁመው የማላልፈው ነገር፤ የሰውን ንቃተ ህሊና
ወይም የማገናዘብ ብቃት ለመግለጽ በተደጋጋሚ የተለያዩ ገላጭ ቃላትን ጨመሬ ብጠቀምም፤ የሰውን ልጅ ንቃተ
ህሊና በአንድ ፈተናና የይወት ተሞክሮ ታይቶ እንዲህ ነው ለማለት ስለሚከብደኝ እኔም አንባቢዬን እንዳላሳስት
አድማሱን ለማስፋት በዚህ መልኩ ለመግለጽ ወሰንኩ።
ጊዜና ሁኔታዎች እየተቀያየሩ ቢመጡም የዚህ ዘመን ሴቶች እህቶቻችንም ከቀድሞዎቹ የተለዩ ናቸው ማለት
አይደልም። ሁሌም ጥያቄው በመኖርና ባለመኖር መካከል የሚንሸራሸር ሆኖ እናገኘዋለን። ሁልጊዜም የማይቀየሩ
ቁልፍ የሆኑ የህይወታቸው መሪ ጥያቄዎች ዘላቂ ደህንነት እና የኢኮኖሚ ዋስትና (Sustainable peace and
Security and Stable Economical Status) ናቸው። እግረመንገዳችንን የምናስተውለው ነገር ታዲያ ይህ
ባህል ሲሆንና ሲደጋገም ይሄው ጠንካራ የሰው ባህሪያችን ተሸካሚው የዘር ሃብል (genetic trait) ለመጪውም
ዘመን የመኖር እድል ያገኛል ማለት ነው። የሚገርመው ነገር ታዲያ በተመሳሳይ ጊዜ ወይም ዘመን ግን ደግሞ በቦታ
ልዩነት ይህንን የሰው ልጅ ባህሪ ወይንም የማህበረሰብ ባህል በተቃራኒው ማየታችን ነው። ለምሳሌ ወደ እኛ አገር
ስንመለስ፤ ሴቶች ምርጫቸው በኢኮኖሚ አቋሙ የተሻለ ሰው ነው። ምንም እንኳን ግለሰቡ ሰርቶ ባያመጣውም
አብሮት የሚገዛው መንግስት እስካለ ሃብታም ሆኖ እንደሚቆይ ታስባለች። ሃብታምና ደህንነቷን ጠባቂ ሰው ነው
ምርጫዋ። የሰውየው የማሰብ ብቃት፣ የሞራሉ ልእልና ጉዳይ ወይንም ስብእና እንዲሁም አካላዊ የሆኑ ነግሮች ሁሉ
እንደመምረጫ አይታዩም። ምክያቱ ደግም ግልጽ ነው፤ የኢኮኖሚያዊና የደህንነት ዋስትናን አመላካች እንዳልሆኑ
ታውቃለችና ነው። ስለዚህ በእኛ አገር አንድ ወንድ ወጣት ሴቶችን ለመሳብና ቤተሰብ መስርቶ ኑሮ መጀመር ካለበት፤
ሃብታምና ደህንነቷን አስጠባቂ ወደመሆን እራሱን በሂደት መቀየር ግዴታው ነው እንደማለት ነው። ምክንያቱም
አጠቃላይ ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ማህበረሰቡ በአመዛኙ ዋጋ የሚሰጠው ሃሳብና እምነት ይሄው የኢኮኖሚና
የደህንነት ጉዳይ ስለሆነ ነው።
የብዙሃን አምባገነንነትና አናሳ ንቃተህሊና (Tyranny of The Majority & Lower Intelligence)
የአናሳዎች የአካልና ስነልቦና ሰለባ መሆን (Mind Control & Genocide)
ጠ/ሚ አብይ አህመድ የዚህን ማህበረሰብ ባህሪ አጥንተው የመጡ ሰው ይመስላሉ (ፓርቲአቸውን ብልጽግና
እስከማለት መድረሳቸውን ስናይ ማለቴ ነው)። ምንም እንኩዋን ጉዟችን የደም ጎርፍ የበዛበት ሸካራ መንገድ
ቢሆንም፤ ማህበረሰቡ ግን የንጹሃን አማራ ብሄር ተወላጆች በብሄራቸው ምክንያት በተገኙበት መታረድ ነገር
ለመጪው ብልጽግናቸው እንደሚከፈል ጥቂት መስዋዕትነት በማድረግ ቀለል አድርገው ሲመለከቱ አይቶ ለተረዳ
ሰው ይህ ነገር (እንደ Tarrany of the majority አይነት ማለት ነው) በማህበረሰቡም ሆነ ተቃዋሚ ፓርቲ
በሚባሉት ዘንድ ስር ሰዶ ያለ ግዙፍ ችግር መሆኑን ይረዳል። ታዲያ እንዲህ ያሉ የማህበረሰብን ባህሪ ቀያሪ ሃሳቦች
27 አመት እንደሆነው ሁሉ አሁንም ድረስ በባሰ ሁኔታ በማህበረሰቡ ውስጥ ለማስረጽ ወይንም ጭንቅላታቸውን
እንደ ኮምፒውተር ፕሮግራም ለማድረግ (Mind Control5
) የአብይ አህመድ የአገዛዝ ስርአት ሚዲያን በበላይነት
5
Mind Control (also known as, Brainwashing, menticide, coercive persuasion, thought control, thought
reform, and re-education) is the concept that the human mind can be altered or controlled by certain
psychological techniques. Brainwashing is said to reduce its subjects' ability to think critically or
Samuel Lakew 10
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
በሞኖፖሊ በመቆጣጠር፤ የኢንፎርሜሽን ፍሰቱን በመገደብ ከራሱ ስርጭት በስተቀር ሰዎች ሌሎችን አማራጭ ነጻ
ሚዲያዎችን እንዳይሰሙ ይህንኑ እነ አዶልፍ ሂትለር የተገበሩትን ፀረ-ሰው ድርጊት በተለያየ መንገድ እየተገበረው
ይገኛል። ልክ ህወሃት ያደርገው እንደነበረ ሁሉ፤ ይህም አገዛዝ መጻህፍትን በመጻፍና በማስጻፍ፣የመዝናኛ
ድርራማዎችና ፊልሞችን ሁሉ ይዘት በመቆጣጠርና በመጠቀም የሚፈልገውን የMind Control ይለፍ ቃላቶችንና
መልእክቶች ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይል እየተገበረው ይገኛል። ይህንንም ‘ድምጽ የለሹ የሰው ልጅን መግደያ መሳሪያ’
ብቻ በማለት እገልጸዋለው። ታዲያ ይሄ ሃሳብ ሲሰርጽ ልምድ ከዛም ቆይቶ እንደባህል ይሆናል፤ ይቆጠራል። ከዚያም
መንግስትም ሆነ ከያንያን ተወቃሽ ተነቃሽም ሳይሆኑ ፊልሙም ሆነ ልብ ወለዱ ‘የገሃዱ አለም ነፀብራቅ ናቸው’
መባሉ ይቀጥላል። እውነትም ልክ ነው፤ አሁን የማህበረሰብ ባህልና ልምድ ሆኗልና፤ እነሱ ዲዛይን ያደረጉት ሰው
ሰራሽ የማህበረሰብ ባህሪ (behaviural modification6
) ለውጥ ልምዱ፣ ባህሉና እሴቱ ሆነው ይቀራሉና።
እውነቱን ከሚያውቀው በቀር ውሸቱ ‘እውነት’ ሆኖ እንደተፈበረከ ማን ያውቃል፤ማንስ ይረዳል? ለመሆኑ እውነትስ
ምንድነው? እውነትንስ ማን ያውቃታል? ማንስ እውነተኛ ሆኖ ይናገራታል?
የፕሮፌሰር ፒተርሰንን ሃሳብ ወስጄ ያገራችንንም ሁኔታ ሳጤነው መሉ በሙሉ ባይሆንም አብዛኛው ተምሪያለሁ
የሚል የአገራችን ወንድ ሰው ለአብዛኞች የኢትዮጵያ ሴቶች እህቶቻችን ለባልነት ተመራጭ አይሆኑም ማለት ነው
ወደሚል አስቂኝ መሳይ መደምደሚያ ልድረስ ይሆን? አስቂኝም አሳዛኝም እውነታ! በዚህ (በኢትዮጵያ) ማህበረሰብ
ውበትና ቁመና፣ ወንዳወንድነትና እውቅት፤ እንዲሁም ተፈጥሯዊ ክህሎትም ሆነ የማገናዘብ ችሎታ ወዘተ
የምንላቸው ነገሮች ሁሉ ከቶውንም ቦታ እያጡ የመጡበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። የተማረ እና ትልቅ IQ ያለው ቢገኝ
እንኳን አገሪቷ ለእንደዚህ አይነት ሰዎች ቦታ ስለሌላትና ምቾት ልትሰጥ የማትችል በመሆኗ ስኬታማ ደልዳላ ህይወት
ለነሱ አይታሰብም፤ ሃብትና ንብረት አያፈሩም ፤ሰርተው አይበለጽጉም። የማህበረሰቡ ሴቶችም በኢኮኖሚያዊና
የወደፊት የደህንነት ዋስትና ሊለግሷቸው የሚችሉ ግለሰቦች ፊታቸውን ያቀናሉ ማለት ነው። እንግዲህ እዚህ ላይ
ከተባለው ሁሉ ደግሞ ተጨማሪ መረሳት የሌለበት ማህበረሰቡ በዘርና በጎሳ መከፋፈሉን፤ በዘር ማሰቡን፤ ማህበራዊ
ግኑኝነቶች ጋብቻን ጨምሮ ሌሎችም ከዘርና ጎሳ እሳቤ ጋር መዛመዳቸውና መሰናሰላቸው የኢትዮጵያን ማህበረሰባዊ
ቀውስ ከምናስበው በላይ የትዬለሌ ያደርሰዋል። ይህ ደግሞ እንደሚደጋገም የህይወት ኡደት (vicious circle)
አሁንም ጭምር ሲቀጥል በመቆየቱ፤ የማህበረሰባችን ስሪት ማያያዣ መልካም እሴቶችና ባህል ቀስ በቀስ እንደክር
እየተመዘዘ በመሄዱ የማህበረሰቡ የራሱም ሆነ የአገርን ውድቀት እጅግ እያፋጠነው ይገኛል ብዬ አምናለው።
ላይ ላዩን የማህበረሰባችንን ያስተሳሰብ ልቀት፤ እይታና እምነት በማየት አንዳንዶቻችን ከምዕራቡ አለም ምን ለየው
ብለን እንል ይሆናል። ከላይ እንደጠቆምኩት ምንም እንኩዋን ገዢው መንግስት ወንጀለኛና በዜጎች ደም ችርቻሮ
የሚተዳደር ነጋዴ መሆኑን ቢያውቁም፤ ወንዶችም ሆኑ ሴቶቹ ለፍላጎታቸው እና የመኖር ዋስትናቸው ሲሉ
ለማንኛውም ሞራል የለሽ ተግባርና የዘቀጠ ስብእና ተገዢ ሆነው እናገኛቸዋለን። የማሰብ ችሎታው ዝቅተኝነት
ከእውቀት መሳሳት ጋር ተደምሮ ለኢሞራላዊ ድርጊታቸው አስተዋፃዖ እያበረከተ ይገኛል። የዚህ ዝቅጠት ውጤት
ለራስም ሆነ ለሌላው ሰው መጪውን አደጋ ሳያገናዝቡ በደመነብስ መኖርን አስከተለ። ይህ ከሌላው አለም የሚለየን፤
independently, [8] to allow the introduction of new, unwanted thoughts and ideas into their minds,[9] as well
as to change their attitudes, values, and beliefs.[10]
6
Is also part of mind control, in fact it is the desired outcome of mind control or brainwashing. It is good to
remember here the CIA mind control program after world war II known by a project code name ‘Project
MKUltra (or MK-Ultra)’. [11]
Samuel Lakew 11
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ታሪካችንም ከሚነግረን እንዲሁም የሃይማኖትና የስነምግባር ሰዎች የመሆናችን ትርክት ጋር አብሮ የማይሄድና
የማይጣጣም፤ የገዘፈ ተቃርኖ ያለው ጉዳይ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ይህ የማህረሰቡ የባህልና ልምድ ፈጣን ለውጥ
ታዲያ ለብዙ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ምሁራን እሳቤ ውስጥ ባለመግባቱ አልያም እየታወቀ በመካዱ ወይም እነሱም
በማህበረሰቡና በአገራችን የቆሸሸ ዘርና ጎሳ ተኮር የውሸት የፌዴራሊዝም ፖለቲካዊ አመለካከት ሰለባ በመሆናቸው
መፍትሄው ላይ እንዳይሰሩ ወይም መስራት እንዳይችሉ አድርጓቸዋል ብዬ አምናለሁ። ችግርን ማመን፤ ለይቶም
ማወቅ (problem identification and acknowledgement) ለመፍትሄው ስኬት ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ
መረሳት የሌለበት መሰረታዊ እውነታ ነው።
ማህበረሰባችን የአንድን የአምነት ተቋም ይመስላል ብዬ አስባለሁ። ከገዢዎቹ የሚነገረውን ሁሉ እውነት ነው ብሎ
የሚቀበል፤ ቃላቸውን እንደ እምነት ቅዱስ ቃል የሚቆጥር የእምነት ቤቱ ምዕመናንን ይመስላል። ገዥዎችም በመጡ
ቁጥር፤ ልክ እንደ ታማኝና እውነተኛ አምልኮ ፈጻሚ ሰው ከመገዛትም አልፎ ያመልካቸዋል፤ እንደ አምላክም ቆጥሮ
ይፈራቸዋል፤ እምነቱን እና ተስፋውን ሁሉ በነሱ ላይ ይጥላል፤ በህይወት የመቆየቱንም እድል በእጃቸው ያኖረዋል።
ለደህንነቱ የሚከፈል ዋጋ ይመስል ታዲያ ማህበረሰቡ በውስጡ አቅፎ ለሚይዛቸውን ጥቂት ንቃተ ህሊናቸው የላቁና
የጎለበቱ የማህበረሰቡ አንቂና ቀስቃሽ፤ የመብቱም ተሟጋቾችን አሳልፎ በመስጠት ቁስሉን እየላሰና በኋላም እየበላ
እራሱን እንደሚጨርስ አይነት ጅብ በመሆን ለራሱም ለነሱም መጥፊያ መንስኤ ሆኗል።
አንዳንዴ ደሞ ማህበረሰባችን እንደ ወታደርም መስሎ ይታየኛል። አድርግ የተባለውን የሚያደርግ፤ አታድርግ
የተባለውንም ለምን ሳይል የማያደርግ። አስፈላጊም ሲሆን ገዢው መንግስት እንደ ኮምፒውተር በቀላሉ ፕሮግራም
በማድረግ ጠላቴ የሚለውን የሚያጠቃበት አደገኛ መሳሪያውም ነው። በወታደር ቤትና ህግ ታዲያ ወታደሩ ‘ለምን’
እና ‘እንዴት’ ብሎ አይጠይቅምና፤ ይህም ማህበረሰብ እንደዛው ሆኖ በማግኘቴ ይሄን አልኩ። የሚጠባበቀው
ከሰመመን የሚያነቃውን የይለፍ ቃል (ወይም pass word) ብቻ ይመስላል። አጨብጭብ ሲባል የሚያጨበጭብ፤
ዝፈን ወይም ጨፍር ሲባልም እንደተባለው የሚያደርግ ማንኛውንም ሶፍትዌር እንደሚቀበል ያለ የኮምፒውተር
ሃርድዌር ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም። ይህን ነገ ሳስብ ሁሌም ወደ አእምሮዬ የሚመጣ ድሮ ልጅ እያለሁ ያየሁት
የሁለት ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ የተጓዙ ልዑል ወንድማማቾች ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን የማይረሳ ፊልም ይታወሰኛል።
የፊልሙም ዕርዕስ “Coming To Amenrica” ይሰኛል። ታዲያ በታሪኩ ውስጥ የንጉሱ ልጅ እንዲያገባት
ከቀረበችለት ሙሽራ ጋር በሰርጉ እለት ባህልና ስርአቱን ጥሶ ከታዳሚው ገለል አድርጎ ጥቂት ጥያቄዎችን
ይጠይቃታል፤ እንዲህም ሲል “ምንድነው የምትወጅው?” እሷም በፍጥነት “አንተ የምትወደውን ሁሉ” ትለዋለች።
ጥያቄውንም በመቀየር “ምን አይነት ነው የሙዙቃ ምርጫሽ?”፤ እሷም አሁንም በፍጥነት በመመለስ “አንተ ምርጫህ
የሆነው ሙዚቃ ሁሉ” ስትል መለሰችለት። ታሪኩን ለማሳጠር ያህል ብዙ ነገር ቢጠይቃትም በተመሳሳይ
ስትመልስለት ልቡ የተሰበረው ልዑል በመጨረሻም የእንሰሳትን ሁሉ ስም እየጠራ እንደነሱ እንድጮህ ቢነግራት
ያለማቅማማት በመጮህ ወደሰርጉ አዳራች እንደ ሽዋዋ ውሻ እየዘለለች የገባችው ነገር እረሳለሁ እንኳን ለሚል ሊረሳ
የሚችል አይደለም። እውነት ነው፤ ሰዎች የራሳቸው ማንነት ፈጽሞ ሳይኖራቸው እንደማየት አሳዛኝና ልብ ሰባሪ የሆነ
ነገር የለም። ኤዲመርፊ ምስጋና ይግባውና የዚያን አፍሪካዊ ማህበረሰብ በእውርነት ተረግጦ የመገዛት ባህል ጥሩ
አድርጎ በትወናው አንጸባርቆታል።
በቃ፤ እውነታው ባይጥምም እንዲህ ነው። አሁን እንዳለው እንደኛ አይነት ማህበረሰብ አገናዝቦና አመዛዝኖ
የገዢዎችን ትክክለኛነት ወይንም ክፋት ማወቅ በዛም መሰረት ምን እንደሚያደርግ መምከር ፈጽሞ የሚታሰብ
አይሆንም። የማህበረሰቡ ንቃተህሊና ዝቅተኝነት እንዲሁምና መሃይምነት ተጨምሮበት፤ መንግስት ለነሱ በውስጡ
Samuel Lakew 12
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ተመችቷቸው እንደሚዋኙበት ያለ የሞቀ ባህር ሆኖላቸዋል። አንድ ቀን ባህሩ እንደሚቀዘቅዝ ወይንም ጭራሽ ደርቆ
ምድረ በዳ እንደሚሆን ከቶውንም አይከሰትላቸውም። ከሆነም በኋላ እንኳን ቢሆን እውነትን ለመቀበል ይቸገራሉ።
በምቾታቸው ወቅት መንግስት ለነሱ እንደ አምላክ ነውና ያለ ነበረና የሚቃወሙት ሁሉ የሰይጣን እና ተከታዮቹ
ጭፍራዎችን ሆነውና ተመስለው ይታዩዋቸዋል። ማንኛውም ከገዢው መንግስት የሚነገሩ ነገሮች ሁሉ ከእምነት
መጻህፍት ይልቅ ይታመናሉ፤ ተቀብለውም ያንኑ መልሰው ያስተጋባሉ። የተግባርም ሆነ የሃሳብ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ
ናቸው። እነዚህን ዝርዝር ችግሮችና የታቀዱ እንዲሁም የታለሙ የስነ ልቦና ጥቃቶች (mind control ወይም brain
wash) ባልገባን ሁኔታ እኛም ማህበረሰቡን እና ወካዮቻቸውን፤ የአንደበቱንም ገላጮቹ ግብዝና አደርባይ እያልን
ስም ብንሰጣቸውም፤ ይህ እንዳለ ሆኖ ነገሩ ግን ከዛም ያለፈና የላቅ መሆኑን መፍትሄው ላይ መስራት ለሚፈልግ
በጎ ምሁር ሁሉ ይህንና ማንኛውንም ተዛማጅና ተያያዥ ነግሮችን አጥርቶ መገንዘብ ይገባዋል ብዬ አምናለው።
በአጠቃላይ ስለማህበረሰብ ስናወራ የምናስበው ወይንም አያይዘን ልናየው የሚገባ ትልቁ ምስል እነዚህ እስከ አሁን
ያየናቸውን ነገሮችና ሌሎችንም ተጨማሪ አካተን መሆን ይገባል። ገዥው መንግስትም ሆነ ደጋፊዎቹ እንዲሁም
ቀሪውም ማህበረሰብ አንድ ላይ የዚህ የትልቁ ማህበረሰብ አካል ናቸው። እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ትክክለኛና ከምንም
የጸዳ የትምህርት እድል ባላገኙና ንቃተ ህሊናቸውም ባልዳበረ ማህበረሰብ አንድ ጊዜ የሚመራቸው መሪ ከተጣመመ
እጅግ አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ። የመጣውን ሁሉ አሜን ብሎ መቀበል ልማዱ ነውና። እንዲህ ያለው ህዝብ ጥሩ
መሪ ይፈልጋል። ብልህና አስተዋይ መሪ ያስፈልጋቸዋል፤ ልክ በጎች ጥሩ እረኛ እንደሚያስፈልጋቸው ያለ፤ ከተኩላ
የሚታደግ ብርቱ እረኛ ለምስኪን እና ደካሞቹ በጎች እንደሚያስፈልጋቸው ሁሉ። እረኛው ቢለግም ግን እሱን
ከመከተል ውጪ ምንም ማድረግ የማይችሉት በጎች መጨረሻቸው የተኩላዎች ሲሳይ የመሆናቸው ጉዳይ ሳይታለም
የተፈታ ነገር ነው። እንደ በግ ለመኖር የወሰነ ማህበረሰብም የመኖርና ያለመኖር ዋስትናው በመሪው ላይ ብቻ
የወደቀ ነው። ታዲያ እንዲህ ያለው ህዝብ ምንም እንኳን ግራና ቀኝ አይቶ ባይራመድም፤ በመልካም መንገድ
ከተመራና ከተኮተኮተ የዘመናዊና ሳይንሳዊ የሆነ ተግባር ከውነው አገርን ባይቀይሩም ፤ እንደ ወታደር የተባሉትን እና
የታዘዙትን ካመኑበትና ከሰለጠኑበት በኋላ ሊተገብሩት ስለሚችሉ ቢያንስ አይራቡም፤ አይጠሙም። አገር በጠላት
ቢወረር እንኳን፤ እንደ አምላክ ቃል የሚሰሙት መንግስታቸውን በመሆኑ ከጥሩ መሪ ጋር ሳይሰስቱ ህይወታቸውን
በመለገስ በጀግነት ተዋድቀው አገርን መታደግ ይችላሉ። አባቶቻችንም በጥበብና በእውቀት ታግዘው ይህን
አድርገዋል፤ እያስተማሩም አንቅተዋል። መልካምንም ባህልና ልምድ ለማህበረሰቡ እያወረሱ የሀገር ፍቅርን እና
ስብእናውን አጎልብተዋል። የማይታመነውንም ከውነው በክብር አልፈዋል። እኔም ሳስባቸው ዛሬን ባለማየታቸው
ታድለዋል ብዬ አልኩ።
“የአቤ ጉበኛ ህመም”
“ጥቅምን ሲያሳድድ ሊደርስ የሚችለውን የማይጠገን አደጋ እያዩስ እነሱም ለምን ይታወራሉ?”
በተቃራኒው ደግሞ አሁን በኢትዮጵያ እያየን እንዳለው የተኩላ ባልንጀራ የመሰለ ገዢ ሲገጥም፤ የመጨረሻው ሰው
ቁጥር እስኪቀር ድረስ አራጃቸውን ያለማስቀየም የያንዳንዳቸውን ቤት አንኳክቶ እንኪመጣ ተራቸውን ይጠብቃሉ።
እንደ በግ በፈቃደኝነትም ህይወታቸውን ይለግሳሉ። በተቃርኖ የሚቆሙ፤ ከማህበረሰቡ የተሻሉና የነቃ አስተሳሰብ
ያላቸው ሰዎች ይህን እብደት አይተው ሊያነቋቸው ቢፍጨረጨሩም፤ ማህበረሰቡ ግን ፍላጎቱ ዋጋ የሚሰጠውን እሴት
ለመጠበቅም ሆነ ለማግኘት ምርጫው መገዛት ነውና የገዛ ማሰቢያ ጭንቅላቱን መብላቱ አደጋው ሳይታየው
አሳቢዎቹንና ድምጾቹን አሳልፎ ለአውሬው ገዢ ይሰጣቸዋል። ይህም ነገር ሲደጋገም፤ የገዥዎችም ጭካኔ ሲበረታ
ለሃገሪቷ ተስፋ ሊሆኗት የሚችሉ የተሻሉ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተመናመነ ይሄዳል። እምነትና
Samuel Lakew 13
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
እስተሳሰባቸውም እንዲሁም ዘራቸው ጭምር እንደዛው አብሮ ይጠፋል። ታዲያ በህይወት ለመቆየት ካለው
አደገኛነትና ምቹ አለመሆን ሳቢያ ከሞት ያመለጠ ገሚሱም ለስደትና እንግልት ይህወት ይዳረጋል። ህዝብና
መንግስትም እንደ እናትና የመጨረሻ ልጅ አይነት ሆነው የእሹሩሩ ህይወት ይቀጥላል። መንግስትም ተብዬው ሲያሻው
በጠዋት ገድሎ ልብ ይሰብራል፤ ከሰአትም ተመልሶ ለቅሶ ደርሶ ልባቸውን ይጠግናል። አዎ፤ ልብ እንደዚህ መቀለጃ
ሆኗል። ሞኝ ህዝብ እና አረመኔ መንግስት ሲገናኙ የሚሆነው ይኸው ነው።
ምንም እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የመንግስት ሃላፊዎች በተዋረድ የማገናዘብ ብቃትና ንቃተ ህሊና (cognitive
ability7
) እጦት ሰለባ ቢሆኑም ትንሽ ብቻ ከሚገዙት ማህበረሰብ በያዙት ስልጣን ሳቢያ በመሻላቸው በግድ
እያሳመኑም ሆነ እያወናበዱ መግዛት ይችላሉ ማለት ነው። እነዚህ መሪዎች በጉልበት እንጂ በሃሳብ መግዛትና መምራት
ስለማይችሉ በማህበረሰቡ ውስጥ የተሻለ ግንዛቤ ላላቸው ጥቂት ግለሰቦች ሃሳባቸውን መሸጥ አይችሉም። ማንኛውም
አይነት የአስተሳሰብ ብልጫና በሃሳብ ልቀት ምክንያት የተጠቁ የሚመስላቸው እነዚህ ባለጊዜ ነን ባዮች ሰዎች
በተመሳሳይ ሁኔታ በሃሳብ የላቀ ምላሽ መስጠት፤ ሃሳብንም በሃሳብ ማሸነፍ ስለማይችሉ አጠቃን ብለው የሚያስቡትን
ግለሰብ ወይንም ቡድን አልያም ያጠቃቸው ከመሰላቸው ግለሰብ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሌሎች ግለሰቦችም ሆኑ
ቁሶችን በመፈለግና ኢላማ በማአድረግ የበቀላቸው ገፈት ቀማሽ ያደርጓቸዋል። ይህን በማድረጋቸውም ከሚሰማቸው
የአደጋና የጥቃት መንፈስ በመላቀቅ የአሸናፊነት ስሜት እንዲሁም ስልጣን በነሱ እጅ ብቻ እንደሆነ ለሚነግራቸው
ውስጣዊ የክፋት ድምጽ ተግዢ በመሆን ለጊዜው ቢሆን እፎይታን ነማግኘት ትንሽ ተንፈስ ይላሉ። እንዲህ ያለውም
ባለብዙ ፊት የሆነው፤ የተዛባው ጎስቋላ ስብናቸው፣ አቋማቸውና ማንነታቸው የማይገባቸውን ስልጣን ጨብጠው
እስከቆዩ ድረስ ለተቺዎቻቸውና ተቃዋሚዎቻቸው እጅግ እደገኛ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። ጠላት ብለው
የሚፈርጁትን ማንኛውንም ግለሰብ ወይንም ቡድን ከቅጣቱ እስኪማር በዚህ መልክ ያሰቃዩታል ወይም ቶርቸር
ያደርጉታል። ይህም ተጎጂውና በቀል የሚሰነዘርበት ግለሰብ ወይም ቡድን በቃ እስካላለ ድረስ ጥቃታቸው
በደጋፊዎቻቸው ጩኸት እየታጀበ ያለማቋረጥ ይቀጥላል። ለተጎጂዎችና ሰለባዎችም ከምንም በላይ ትናንት ለፍትህና
ለዲሞክራሲ ታገልን ሲሉ ከነበሩ ሰዎች የዚህ ክፋት ተባባሪ እንደመሆን የሚያም ነገር የለም። ይህን ህመም “የአቤ
ጉበኛ ህመም” ብዬ እጠራዋለሁ። ይህንንም ለምን እንዳልኩ ጥቂት ዘለቅ ስትሉ ሁሉም ይገለጥላችኋል። ደራሲው
አቤ ጉበኛ በደርግ ጊዜ የማህበረሰቡን የዋህነትና ሞኝነት እንዲሁም የገዥዎችን ክፋትና የደጋፊ
አጨብጫቢዎቻቸውንም ታሪክ በመልካም ብዕሩ ከትቦ ባያስቀርልን ኖሮ የእሱ እይታ ምስክርነት ከወዴት ይገኝ
ነበር እያልኩ ትንቢታዊ መሰል ጽሁፎቹን ለዘመኑ አስደናቂ ማስረጃ ነውና ብደብቀው ታሪክም እንዳይወቅሰኝ ጥቂት
ልጠቅስ የግድ ሆነብኛል። የሁለት ዘመን አንድ ማጣቀሻና ማስረጃ!
አቤ ጉበኛው በ 1965 ዓ/ም ከፍተኛ ትምህርቱን ለመከታተል ቢሄድም ከአመት በኃላም በመፈንቅለ መንግስቱ
ምክንያት ለውጥ መቷል ሲሉት ሁሉን ትቶ ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: አቤም በ1966 ዓ/ም ሁኔታውንም ታዝቦ ይህን
በማለት በገዛ ብዕሩ የሚከተለውን ከትቦ ነበር::
7
Cognitive ability በጎግል ፍቺ መሰረት “የግንዛቤ ችሎታ” ሲል ይፈታዋል። በእውቋ የስነልቦና ተመራማሪ Linda Gottfredson [12]
ትርጓሜ መሰረት ደግሞ፤ የእውቀት (ኮግኒቲቭ) ችሎታ በአመክንዮ የማሰብ ፣ እቅድ የማውጣት ፣ ችግሮችን የመፍታት ፣ በጥልቀት የማሰብ
፣ ውስብስብ ሀሳቦችን የመረዳት ችሎታ ፣ በፍጥነት መማር እና ከልምድ መማርን የሚያካትት የአእምሮ ችሎታ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።
[Cognitive ability may be defined as a mental capability that … involves the ability to reason, plan, solve
problems, think abstractly, comprehend complex ideas, learn quickly and learn from experience.]
"በአገራችን ላይ የለውጥ እንቅስቃሴ መጀመሩን ሰማሁ፡፡ ከሰማኋቸው ወሬዎች በተረዳሁት መሠረት ሁኔታው
መልክና አቅጣጫ የሌለው ወደ ደም መፋሰስ የቀረበ ሆኖ ታየኝ፡፡ ወደ አገሬና ወደ ቤተሰቤ ተመልሼ ሞቱንም
ሽረቱንም ከአገሬ ሕዝብ ጋር ከመካፈል የበለጠ ተገቢ ዕድል እንደሌለኝ በማመን ወደ አገሬ የምመለስበትን
ቀን ለማፋጠን ወሰንሁ፡፡ የጥናቱን ባይሆንም ከጉብኝት ጊዜዬ ቀሪውን አቋርጬ ወደ አገሬ ተመለስሁ።” [13]
Samuel Lakew 14
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
የተከብረው አቤ ጉበኛ ታዲያ አገር ቤት ገብቶ ሁኔታውን ሁሉ ቢመለከት ጊዜ ለውጥ የሚሉት ነገር እንደኛ እንደ
እሁኑ ዘመን የልጅ እቃቃ ጨዋታና ነፋስ ማባረር አይነት መሆኑ ገባው:: ትችቱንና ተቃውሞውንም በጋዜጣ መጻፉን
ቀጠሎ ነበር:: የደርግ ስልጣኑን በሃይል መቆጣጠሩ አልጥምህ ያለው አቤ ታዲያ በቀልድ እያዋዛ መልእክቱን በቲያትር
መልክ ፅፎ ለታዳሚዎቹ ያቀርብ ነበር:: ከድርሰቶቹም ውስጥ "ፖለቲካና ፖለቲከኞች" የተሰኘው በዋናነት ይጠቀሳል::
ሰዎች አቤ የሚፅፈውን ነገር ሁሉ እየተከታተሉ ፖለቲካ ነው የሚጽፈው በማለት የዘመኑ የደርግ አጨብጫቢዎች
ቁም ስቅል ያሳዩት ነበር። መተቸትና የማይሆነውን መቃወም ዛሬ የተጀመረ አይደለምና፤ እንደኛው እንዳሁኑ ዘመን
ያሉ የደርግ ታማኝና እርኩስ ቡቹሎችም የሚፅፈውን አይወዱለትም ነበር:: ታዲያ እንደዛሬ አፋጣኝ መልስ
የሚሰጥበት ቲውተር ወይንም ፌስቡክ ያልነበረበት እንዲሁም ያልታለመበት ዘመን በመሆኑ እቤ በጋዜጣው እድሉን
በመጠቀም ለተቃውሟቸውና ክሳቸው እንዲህ ሲል እስከ እሁንም እጅግ ገራሚ የሆነ መልስ መስጠት ግድ ሆኖበት
ነበር።
አዎ፤ በ 1955 ዓ/ም የተደረሰው “አልወለድም” እና የበርካታ መጽሃፍቶች ደርሲ አቤ ጉበኛ የዘመኑ ነብይ ነበር:: አቤ
ትንቢተኛ ነበር:: የዛው ዘመን ነቀዞች ተቃዋሚዎቹና አስገዳዮቹ ዛሬም አፍርተውና ተባዝተው ፤ ፍትህና ጥበብ ጠል
ዘራቸውንም ከትውልድ ትውልድ አውርሰው እነሆ አሁንም እነሱ አእምሮ አልባ ሆነው ሌላውንም የነሱ አምሳያ
አድርገው በመቅረጽ ወደ ወድቀታቸው አንደርድረው ከጣሏቸው ከራረሙ:: አቤን አትተንፍስ እንዳሉት እኛንም ዛሬ
ይሉናል:: አቤ ትንቢተኛው ብዕርተኛ እንዳለውም ሆነና ዛሬም ለሰባዊነት፣ ለፍትህና ለዲሚክራሲ ታግለናል እያሉ
በአደባባይ እየደሰኮሩ ሲያደነቁሩን የከረሙት ሊቅ እና ምሁር ነን ባዮች ዲሞክራሲ ያሉትን ትቼ ፍትህንና ሰባዊነትን
ከሚያዋርዷት ጋር እነሆ በፍቅር ወድቀው በአይናችን በብሌኑ ተመልክተን ለመታዘብ በቃን:: አንሶላም ተጋፈው
እርኩሰታቸውን ፈፅመው ሲያበቁ የኛዎቹም ጉዶች እነ ግርማዊ ጭጭ ይበሉና እነ አፈ-ንጉሥ አይተንፍሱ እኛኑ
መልሰው በመቃወም "ሰው ሲሞት አትቃወሙ፤ ፀጥ በሉ። ለናንተም ሆነ በህይወት ላሉትም አይበጅም:: የናንተ
ተቃውሞ ነው ግድያውን የሚያባብሰው" በማለት ህሊና ቢስነታቸውን እና ፀረ-ሰብአዊ አቋማቸውን ሳይደብቁ
እያሳዩን ‘በሰው ቁስል . . .’ እንደሚሉ የቆሰለውን ልባችንን እየነካኩ እንዲመረቅዝ ማድረጉን ተያይዘውታል።
"ይህ ቲያትር የተጻፈው የምንም ዓይነት ፍልስፍና ማስፋፊያ ወይም መቃወሚያ እንዲሆን አይደለም።
ዋና አላማው የአገራችን ለውጥ ተጀምሮ እየገፋ በመጣበት አንድ ጊዜ ላይ የታየውንና አሁንም ባንዳንድ
ሰዎች ላይ የሚታየውን ቅሌትና አሳሳችነት ለሕዝብ ገልጾ ለማሳየትና ፍርዱን ለባለ ጉዳዩ ሕዝብ
ለመተው ነው፡፡ ... ከእነዚህ ሰዎች አንዳንዶቹ ከግል ትችት አልፈው በጋዜጣ፣ በመጽሔት፣ ወረቀት
በመበተን ለማሳጣት ሞክረዋል፡፡ ሰሚ ቢያጡ እንጂ “ፀረ ሶሻሊስት፣ ፀረ አብዮት፣ አድሃሪ” ሲሉኝ
(መንግስት) ምን እንዲደረግብኝ መፈለጋቸው ኑሯል? በነሱ ቤት አንድ ሰው ምንም ያህል ለሀገሩ
ጠቃሚ ይሁን፣ ምንም ያህል ወገኖቹን ይውደድ በእነርሱ አስተሳሳብ ካልተስማማ መኖር የማይገባው
ሰው ነው፡፡ . . . አንዳንድ ሳዲስቶች (በሰው ስቃይ የሚደሰቱ ጉዶች) እንደሚመኙት ከወገኖቼ በአንዱ
እጅ ብሞት እንኳ በዚያ ዕብድ ጭካኔ የብዙዎች ወገኖቼን ቅን መንፈስ ለውጬ አላየውም፡፡ ያለኝን
ያህል ችሎታና ዐቅም ካስፈለገም ሕይወቴን ጭምር ለሀገሬ ከማበርከት ከቶውንም ወደኋላ
አያሰኘኝም፡፡ ...አሁን ችግር የሆነብን በአገራችን ሁኔታዎች ላይ የምንመለከታቸውን ችግሮች
እንዳንወያይባቸው ለምን ትንፍሽ ብላችሁ ማለታቸው ነው፡፡ ለመሆኑ እነግርማዊ ጭጭ ይበሉና እነ
አፈ-ንጉሥ አይተንፍሱ እንደሚመኙት ሁሉ ሥልጣን የነሱ ቢሆን ኖሮ ምን ሊሠሩ ኑሯል? ለነጻነት
ለዕኩልነትና ፍትህ ስንታገል ኖርን የሚሉ ሰዎች ለምን ሀሳብን በመጨቆን ያምናሉ? ጥቅምን ሲያሳድድ
ሊደርስ የሚችለውን የማይጠገን አደጋ እያዩስ እነሱም ለምን ይታወራሉ? እኔ ግን ማንም ዋሾ ይጥላኝ
እንጂ ያየሁትን መግለጼን መተውን እንደከፍተኛ ሀገርን መካድ ስለምቆጥረው ያየሁትን እውነት
በቀልድ መልክ አቅርቤላችኋለሁ፡፡" [14]
Samuel Lakew 15
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
የአደርባይነት ልካቸው፤ በድሃው ህዝብ ሞት፤ ዘሩ አማራ ነው እየተባሉ በህጻናቱም መታረድ የመሳለቃቸው ነገር
ሁሉ አንድ ላይ ሲታይ ከአቤ ዘመን ይልቅ የአእምሮ መጨንገፉም ሆነ የሞራል ልዕልናው በብዙ ጎልብቶ መላሸቁ
አሁን የሚያስፈራ ደረጃ ላይ መድረሳችንን አመላካች ማሳያ ነው። ያኔም የነበረው አደርባይነት አሁንም ተባብሶ አድጎ
አለ። ያኔ አቤ በ“አልወለድም” ድርሰቱ የተረከው የህዝብ አእምሮ ማጣት፤ የገዢዎችም አረመኔነትና ነገን የሚያይ
አዙሮ ማሰቢያ ማጣት የደመነብስ ተጓዥነታችንን ያጋልጥብናል። አቤም ለነገ ሳይል ይህል ብሎ በ”አልወለድም”
ድርሰቱ ልቦለድ አስመስሎ እምቁን ስሜቱን በመጻፍ ተነፈሰው። ገጸ ባህሪያትንም ፈጥሮ በራሱ አንደበት ትንቢትን
አናገራቸው። ሁሉም እውነት ነበረ። በጊዜና ቦታ የማይወሰን እውነት!
እንዴት የአቤ ጽሁፍ መልእክቶች ሁሉ የኛን ዘመን አጉልተውና ቁልጭ አድርገው ሊያሳዩ ቻሉ? ይህ የዘወትር
ጥራያቄዬ ነው። ለራሴም ዘወትር የምመልሰው መልሴም ዘመን ተቀየረ እንጂ አየሩም ሆነ ህዝቡ ያው ነው የሚል
ነው። ማህበረሰቡ እራሱን በራሱ እያየና አምሳያውን እየተካ ቢያልፍም መንፈሱና አስተሳሰቡ ግን እንዳላለፈ ማሳያ
ነው። እነ አቤ ጉበኛ እና መሰል ጓደኞቹ ግን ዛሬ በመንፈስም በስጋም የሉም። ብዙዎቹ ዘራቸውን እስኪተኩ
አልተጠበቁም። አዎ፤ እነሡማ አይናቸውን በአይናቸው እንዲያዩ አልተፈቀደላቸውም። እነሱ የአስተዋይና እና
የጥበበኛ ሰዎች ዘር እንጂ የብሄርና ጎሳ ዘር የላቸውምና፤ ከማንም በላይ ልቀው ለክፉዎች፣ ለደካማ ሸውራሮችና
ለጨለምተኞች ስልጣን ላይ መቆየት ስጋት በመሆናቸው እየተሳደዱ በዘመናት ሁሉ እስከአሁኗ ሰአት ይታደናሉ።
ይገደላሉ። ዘርና ጎሳ እንዲሁም የአንባገነኖች ድንፋታ አይገባቸውምና አምርረው ይጠሏቸዋል። ጥበባቸውንና
እውቀታቸው እንደ ክፉ መንፈስ ቆጥረውባቸው እያስቆጠሩ ዘራቸውን ያጠፉታል። የአእምሮተኞች ዘር ማጥፋት
ዘመቻም ዛሬም ድረስ ገዥዎች ትኩረት ሰጥተው በትጋት የሚሰሩበት ጉዳይ መሆኑ ለዚያ ነው። ለደናቁርት መሪዎች
ይህን ሲያደርጉ ከዛሬ ይልቅ ነገ እየተሻለ የሚሄድ ይመስላቸዋል። እውነትን እንደመሰላሸው በስሜታቸው
ይለኳታልና ህይወታቸው በስህተት የተሞላ ነው። አያስተውሉምና ከስህተታቸውም አይማሩም። ከአውሬም በላይ
አውሬ አለና፤ ከህሊና ቢስ በላይ ህሊና ቢስ ሞልቷልና ኮትኩተው ያሳደጓቸው ጨካኝ አዞዎች አንድ ቀን ፊታቸውን
እስኪዞሩባቸው ብቻ ይሆናል የእድሜ ገደባቸው።
የአቤ ጉበኛን ‘አልወለድም’ መጽሃፍ አባቴ በትንሿ ሼልፍ ለአቅመ ንባብ እስክበቃ ደርድሮ ከቆየኝ መጽሃፍቶች
ውስጥ አንዷ ነበረችና ሁሉም ባይገባኝም፤ ያነበብኳት ግን ገና በጠዋቱ ነበር። ለዛም ይሆን አላውቅም አንዳንዴ
“አዲስ ወታደራዊ መንግሥት በሚሰብክበት ጊዜ ህዝቡ በየቦታው ተስፋውን እየተመገበ ይፈነጭ ነበር፡፡ በየጊዜው
ወደከተማ ስመላለስ እንዳየሁት ሕዝቡ አዲሱን መንግሥት ያላንዳች መቃወም ተቀብሎት ነበር፡፡ የባላገሩ ኗሪም
ምንም አልተቀንቀሳቀሰም ነበር፡፡ ነገር ግን ከጊዜ በኋላ አንድ ሁለት ዓመት ቆይቶ በገበሬው በነጋዴው በባለ
ኢንዱስትሪውና በሌላውም ሠርቶ ኗሪ ህዝብ ላይ ግብርና ቀረጥ እየተደራረበ ለጦር አለቆች መቀማጠያ ለጦር
መሣሪያዎች ማደርጃና ማብዣ ሆነ፡፡ የሕዝቡም ጠቅላላ ኑሮ ሰላም ከማጣቱና መንሰራፊያ ከመሆኑ በቀር ከድሮው
በምንም አልተሻለ፡፡ ... ለሥልጣንና ለሹመት የሚመረጡት የጦር መኮንኖች ብቻ ስለሆኑ ስንቱ አዋቂ በንግድና በእርሻ
ሥራ ራሱን ለመርዳት ካልሆነ በቀር በመንግሥቱ ድርጅቶች ገብቶ የሥራ ተካፋይ ለመሆን ዕድል አጣ [15]።
የኛዎቹ አዲስ መንግሥት መሥራቾችም በኃይል ጭጭ አድርገው እየገዙን እያየን ‘አገራችንን ከጭቆና አገዛዝ ወደ
ነጻነት መራናት’ እያሉ ይፎክሩብናል፡፡ ይኸውም የጊዜውን ነፋስ በመከተል ነው፡፡ ... ለውጡ የትኛው ነው? እናንተ
ለውጥ ብላችሁ የምታምኑት የጥቂት ሀብታሞችን መሞትና መንገላታት ነው? እኛ የምንፈልገው እንዳይጎዱንና
እንዳያጠቁን እንጂ እነሱ ቢሞቱ ደማቸውን አንጠጣው፤ ቢሰቃዩና ቢንገላቱ የመንፈስም ሆነ የአካል ደስታ አናገኝበት!
ወይስ መሻሻል የምትሉት ሲቪል ሹም ሽሮ ወታደራዊ ሹም መሾሙን ነው? ወይስ ከሕዝብ አንዱ ድምጽ ሊሰጥበት
የማይችለውን ለስሙ ግን የህዝብ መንግሥት (ሬፑብሊክ) የሚባል መንግሥት መቋቋሙን ነው? ኧረ ለውጥ
የምትሉት የቱን ነው? ድርብ ቀረጥና ግብር መክፈሉን ነው? ጠቃሚ ድርጅቶችን እያደከሙ ለውጭ ጠላት እንኳ
ሳይሆን ያገርን ሕዝብ ለማጥቃት የጦር ድርጅቶችን ማስፋፋቱን ነው? እንግዲህ አዲሱ መንግሥት ያሳየን ለውጥ
ይህን ነው፤ ይህን ከሆነ መሻሻል የምትሉት ሌላ ነገር ነው [16]፡፡
Samuel Lakew 16
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ሳስበው ልክ ከአቤ ጉበኛ ጋር በዚያ ዘመን በአንዳች ሃይል ጊዜውን አዛብቼ፤ ከጊዜው ቀድሜ አልያም እሱ ወደ እኔ
ጊዜ መቶ የመከረኝና አልወለድምን ሲጽፍ ያማከረኝ፤ አብሬውም የጻፍኩም ይመስል የክስተቶቹ አዲስ አለመሆን
ይገርመኛል። ክስተቶች ያው ናቸው። ሰዎችም እንደዚያው። ጊዜዎች ግን ያምታታሉ። አንዴ 1950ዎቹ፤ ሌላ ጊዜ
ደሞ 1960ዎችና ሰባዎች፤ መልሶ ደሞ አሁንና 1990ዎች። ክስተቶቹ የመጀመሪያቸው አለመሆናቸውን፤ ቀድመውም
በህይወቴ እንደሆኑ ያለ ያለመገረም ስሜት ይሰማኛል። ለዚህ ነገር ገላጭ የሆነው ቃል ከፈረንሳውኛ በስተቀር
በሌሎች ቋንቋዎች አይገኝምና ጠቁሜችሁ ልለፍ። ቃሉ ‘ዴዣቮ’ ወይንም በፈረንሳይኛ ሲጻፍ (déjà vu8
) ይሰኛል።
የአእምሮ ጄኖሳይድ (Intellectual Genocide) በኢትዮጵያ
በመጨራሻም፤ ያነሳኋቸውን ነገሮች በአእምሯችን ይዘንና ጨምቀን፤ አንድ ላይም አያይዘን አንዱን ካንዱ ሳንነጣጥል
ብናብላላቸው እንደሚከተለው ወደ መደምደሚያችን መንደርደር እንችላለን። በነዚህ የጠቀስኳቸውና ያብራራኋቸው
አመክንዮአዊ ሙግቶቼ መሠረት ከሄድን እንግዲህ የዚህ የኦነጋዊ መር የኦሮሙማ መንግስትም ሆነ የቀድሞው የወያኔ
መር መንግስት ቁጥር አንድ ጠላት ምሁሩ ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም። አሁንም ግልጽ ለማድረግ ያህል፤ ምሁሩ
ስል የነቃ መንፈስ ያለው፤ የተማረው፣ ከብዙሃኑ የተሻለ ክፉውንና ደጉን ለይቶ የሚያስብ፣ ምን እየተከወነ እንደሆነ
የሚያውቀውና የሚከታተለው፣ ለምን እና እንዴት ብሎ የሚጠይቀው፣ የሚተቸው፣ የሚወቅሰው፤ የገዢዎችን
ወንጀል የሚያጋልጠውና ለአገርና ለህዝብ ደህንነት የሚጨነቀውን ክፍል ማለቴ ነው። እናም ከብሄር ይልቅ በባሰ
መልኩ ምሁርነት የነዚህ እና የቀደሙት ጥቂት የአገዛዝ ስርአት ተቀዳሚ ጠላቶች ነበሩ፤ ዛሬም ናቸው እያልኩ ነው።
‘ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው’ እንደሚሉት ብልሆቹ አባቶቻቸን፤ እነዚህ ሰዎች የሚፈሩት የሚጠሉት የሚያወራን፣
የሚጽፍን፣ ማስረጃን በፎቶና ካሜራ የሚያስቀርን፣ ሂሰኛንና ተቺን፣ ወንጀላቸውን ለአለም የሚያጋልጡትን ወዘተ
ነው። ለዚህም ማስረጃ ለመጥቀስ የቀድሞው ሟች ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በ1993 ዓ/ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአንድ
ጊዜ 42 የሚሆኑ የሃገሪቱን ምርጥ ምሁራን ፕሮፌሰሮችን እና ዶክተሮችን ጠራርጎ ማባረሩና ብዙዎችንም እያሰረ
ማሰቃየቱ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው [18]። ወያኔ መሩ የቀድሞው ኢህአዲግ የተሻለ የተባለውን የትምህርት ስርአቱን
በተመሳሳይ ሁኔታ መግደሉና ማበላሸቱ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱንም የዚህ የዘር ተኮር የጎሳ ፖለቲካው
አይዲዎሎጂ ፕሮፓጋንዳ ማስፋፊያና ማሰልጠኛው ማድረጉ ዛሬ የደረስንበት እጅግ ወደባሰው የማህበረሰብ የሞራል
ልእልና አንዲሁም አስተዋይነት መሞት፤ በዚሁም ሳቢያ ለመጣው የሃገር ውድቀት ትልቁን ድርሻ ይደስዳል።
በተመሳሳይ መንገድም የመለስን ህልም ተርጓሚውና ራእይ አስፈጻሚው፤ የስም ለውጥ ብቻ ያደረገው አብይ አህመድ
ክፉኛ ታሞ የነበረውን የትምህርት ስርአት ሙሉ በመሉ በመግደል አፈር የማልበስ ስነስርአት ላይ ይገኛል። ለዚህ
ማሳያ ይሆን ዘንድ አንድ ትንሽ ተራ ማሳያ ብቻ እንኳን ብናይ፤ አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት ባሳየው የህክምና
ባለሙያዎችን የማራከስ፣ የመናቅና የማንቋሸሽ ተግባሩ የዚህን መንግስት ባስ ያለ ፀረ ምሁርነትና ፀረ-ትምህርት አቋም
መገለጫው ያደረገ መሆኑን ነው። ታዲያ ማህበረሰቡ በሽታውን እንኳን ለሚያክሙት ሃኪሞች አለመሟገቱና
እንዳልሰማ አንዳንዴም እንደ ወንጀለኛ አይቶ ማለፍ በነሱ ላይ መፍረዱ የገዢዎች መሳሪያነቱን ያመላክተኛል።
ማህበረሰባችን ደጋግሜ አንዳሉት እውነትን አመዛዝኖ መያዝና ለነገ ማቀድ መገለጫው ባለመሆኑ፤ ስጋቱን እና
ውድቀቱን አይተው ሊያድኑት ህይወታቸውን አስይዘው ከገዢው መንግስት ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ሲተናነቁላቸው
የነበሩትን፤ በአማራው ተወላጅና የኦርቶዶክስ አማኞች ላይም እየመጣ የነበረውን የዘር ፍጅት አደጋ እቅድ ሲያጋለጡ
የቆዩትን እንደ እስክንድር ነጋ ያሉ የነጻነት ታጋዮችና ጀግኖች ያለምክንያት በግፍ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ በእስር ቢቆዩም፤
8
Déjà vu (Noun): A feeling of having already experienced the present situation. (Oxford Dictionary)
Samuel Lakew 17
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ከላይ በዘረዘርኳቸው ምክንያቶች እስራቸውን እና ግፋቸውን ለምን ብሎ የሚጠይቅላቸው ተቆጪ ማህበረሰብ
እንደሌላቸው ሲታይ እጅግ ልብ ቢሰብርም፣ ቢያሳዝንም፣ ሊገርመን ግን አይገባም። ‘ለአዲስ አበባና ለመላው
የኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ከፍለው እያለ፤ የማህበረስቡ መልስ ለምን ዝምታ ሆነ?’ ብለው ለሚገረሙና
እስክንድር ነጋ እና አስቴር ስዩም (ሁለቱም ሰዎች እስከዚህ ቀን 05 ጃንዋሪ 2021 ድረስ በኢትዮጵያ እስር ቤት ሳይፈረድባቸው ታስረው ላይ ይገኛሉ)
ለሚጠይቁ ግለሰቦች አሁንም መልሱ ይኸው ከላይ እንደተገለጸው ከውስን ግለሰቦች በስተቀር ማህበረሰቡ በፍርሃትም
ይሁን በመስማማት ፈቅዶና ወዶ ከገዚዎች ጋር ማበሩና መተባበሩን በዝምታ መግለጹ ነውና፤ ይህንን አምኖና
ተቀብሎ ማህበረሰቡን ከከባድ እንቅልፉ ለማንቃትና ለመቀስቀስ የተሻሉ መንገዶችን ተመካክሮ መዘየድና መፍትሄ
መፈለግ ተገቢ ነው ስል ምሁራንን አጥብቂ እመክራለሁ።
የመንግስት ተቺ እና ተቃዋሚ ለሆነ ሰው እንደ 1930ዎቹና እንደ 1940ዎቹ የምስራቅ የጀርመን ወጣቶች አይነት (ከ10
የቤተሰብ አባል ምስራቅ ጀርመኖች 6ቱ የመንግስት ጆሮ ጠቢ ነበር) ስጋቱ ከማህበረሰብም አድጎ ወደ ቤተሰቡ
ጭምር መድረሱ አይቀሬ ነው። የመንግስት ቁንጮ ላይ ያለው ግለሰብ በህዝብ መገናኛ ሚዲያዎች አስተውሎ
ለሚያዳምጥ ሰው ለወላጆችም ጭምር በልጆቻቸው ላይ ተፅዕኖ እንዲፈጥሩ በሚያስደርግ አስገዳጅ የፕሮግራም
ቃላት (mind control) የታጨቁ መሆናቸውን ይገነዘባል።
በአጠቃላይ ሲታይ እንግዲህ፤ እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ ከገጠመን እንዲህ ካለ ውስብስብና እጅግ ጥልቅ አዘቅት
ገደልና ጨለማ ለመውጣት የሚረዱን ችግር ፈቺዎች ያስፈልጉናል። ችግሮችን የሚፈቱልንን አቅም ያላቸውን
ማንኛውንም አይነት ሰዎች እኔነታችንን በመተው በትእግስና በትህትና ወርደን በመፈለግ አብረንናቸው ልንሰራ
ይገባል። መሪውን ልንሰጣቸው ይገባል። በዘር ሳይሆን በውቀትና በተሻለ ባሰበ ስንመራ፤ ሁላችንም
እንደየመክሊታችን ልንሰራና የአቅማችንን አስተዋጽኦ በማድረግ አገርን በትብብር አሳድገን በሰላም ለመኖር መወሰን
ትልቁ ማስተዋል ነው ብዬ አምናለው። እስክንድር ነጋን እና መሰሎቹን እየተቃወመ እስክንድርን ካልሆንኩ ለሚለኝ
ቅናተኛ ሰው አትችልም ከማለት ወዲያ ምን እለዋለው? እንደ እስክንድር ነጋ ያለ ድፍረት፣ አርቆ አስተዋይነትና
እኔነት አልባ ሆኖ ለሌሎች ያደረ መሆን መኖሪያውን እስር ቤት ቢያደርግበትም፤ ከአምላክ የተሰጠው ነውና ይህን
ለመሆን አይጥርም። እኛም የውስጣችንን እስክንድር እንፈልገውና ለሌሎች ብልህና አስተዋይ ሆነን እንኑር። በየሙያ
መስኩ ያሉ ልሂቆቻችንን ካልተንከባከብን መጨረሻችን እንደሶሪያና አፍጋኒስታን እንደ ጀመርነው ተበላልተን
እንዳንጠፋ እንጠንቀቅ። የተከፋፈለች አገር ልኡዋላዊነትን ጠብቃና አስከብራ መኖት አይቻላትም። የሱዳን ወረራና
የመንግስት ዝምታ ለኢትዮጵያ መውደቅ አመላካች ነገሮች ናቸው። ዝምታ ደሞ ትርጉም አለው። መሬቱ ተሽጦ
Samuel Lakew 18
Psychology – Science topic
RESEARCH GATE: 05 January 2021
ORCID: 0000-0001-7272-1470
ወይም አገሪቷ እንዳለች እንደቁም ከብት በቁሟ ተሽጣ ሌሎች ቢያዙባትስ ምን ይታወቃል። ነገ ደግሞ ማን መሬት
አለኝ ብሎ ይመጣና ይወረን ይሆን? የቻለውን ሁሉ ዘርፎ መገብጠልንም ምርጫው አድርጎ በሚያስብ የወራሪ
መንፈስ ተላባሽ መንግስት እንዴት ተአማኒ ይሆናል? የምናየውንና የምንሰማውን ሁሉ ወስዶ ማገናዘቡና ተገቢውን
ውሳኔ መወሰኑ ለመኖር ህልውና ወሳኝ ነው። የሁላችንም እኩል መጠለያና መኖሪያ የሆነች አገር እንደምታስፈልገን
ገብቶን ከሆነ፤ ትንሽ የምናስተውና አርቀን መጪው ማየት የቻልን ሁሉ ስንሰማ ያደግናቸውን አእምሯችንን
ያላሸቁትን የዘረኝነትና የጥላቻ ፈጠራ የፕሮግራም ትርክቶች (brain washing) ወደጎን በመተው መነጋገርና ወደ
መግባባት በመምጣት አገርን እና ወገንን ወደ ማዳን ወስነን እንቁረጥ ብዬ እኔ በዚህ ጽሁፌ በታናሽነትና አክብሮት
ዝቅ ብዬ የሚመለከታችሁን ሁሉ፤ የተከበሩ አንባቢዎቼንም እንዲሁ ጨምሮ እጠይቃለሁ። ከኛ የሚጠበቀው በበጎ
ህሊናና በቅንነት መደማመጥ፣ መስማማትና መተማመንንም ወዘተ ብቻ ነው።
እስከዛሬ እንዳለው በሽታችን ያለ ነገር፤ “እኔ ብቻ ልሰማ፤ እኔ ብቻ ልደነቅ፤ እኔ ብቻ ልታይ፤ እኔ ብቻ ልስራው፤
ከዚህም ጋር ተያይዞ የሚመጣውን ጥቅማ ጥቅም ሁሉ እኔ ወይም እኛ እናግኝ ምክኛቱም ተራዬ ነው፤ ጊዜዬ ነው፤
ከባለጊዜው ጋር ልመሳሰል፤ ለሚታረደው ምን አገባኝ ወዘተ” የሚል በበዛበትና ድንቁርና በነገሰበት በዚህ የአገራችን
የጨለማ ወቅት እንደ እስክንድር ነጋ ያሉ ሰዎችን በባትሪ ፈልጎ ማግኘት ከዛሬ ነገ እጅግ እየከበደ ይሄዳል ብዬ
አስባለሁ። የወደፊቷ ኢትዮጵያ መኖር ከቻለችና ከወደቀችበትም መነሳት እንዳለባት ካመንን ማገናዘብና ማሰብ
የሚችሉ፤ ንቃተ ህሊናቸው የላቁ፤ ምንም ይሁን ምን ለዚህ ለማይደግፋቸው ማህበረሰብም ቢሆን ችግሩን
ተገንዝበው እራሳቸውን እንደ መስዋእት በግ በማቅረብ ከሞት ጋር የሚተናነቁ ሌሎች እስክንድሮችና መስከረሞች
(መስከረም አበራ)፣ ሌሎችም እንደ ኢንጂነር ይልቃሎች እና ልደቱ አያሌዎች ብዙ ብዙ ያስፈልጉናል። ሌላውን
እንኳን ማድረግ ባንችል አቅም ያላቸውን እንደሚያስፈልጉን በማመን አስተዋይነትን መግለጽ ብልህነት ነው። ማዕበል
ሲነሳ ብቻ መርከቧ እንዳጸምጥ እውነተኞዙን የየሙያ መሪዎች እያለቀሱ መፈለግ ሁሌም መፍትሄ አይሆንም።
ማዕበል ሳይኖርም እንዲመሩን እንፍቀድላቸው። ይህን ባናደርግ ግን አንዳንዴ ድንገት ከተፍ የሚለው ማእበል
ሁላችንንም ጠራርጎን እሊሄድ እንደሚችል አሁን እናስብ። ለሚታረዱት ምስኪን የአማራ ተወላጆች ዛሬ ሎቻችንም
በጊዜ ሳይረፍድና ወደኛም ሳይመጣ እንጩህ፤ እንቃወም። ብንችል ከሰባዊነትም እንጻርና ቃሉ እንግዳ ቢሆንብንም
የአንድ ሀገር ዜጎች እንዳላቸው የብሄራዊነት ስሜት ጤነኛ መተሳሰብ ኖሮን አንድነታችንን እናጠንክር። አንድነት
ማለት የትርክቱ ‘አሃዳዊነት’ ሳይሆን ትርጉሙ እንደዚህ ባለው ወቅት፤ የውስጥም ሆነ የውጪ ወራሪዎች ሲከቡን
ብቻ የምንረዳው ነገር ይመስለኛ። በአማራ ህዝብ ላይ እየሆነ ያለው ጭፍጨፋና ጥቃት አሳዛኝ ነው። አሁንም አማራን
ለማጥቃት በሚመስል መልኩ አገሪቷን አብይ አህመድ በሱዳን ጓደኛው አማካኝነት አስወርሮ ለአማራው በክልሉም
ጭምር ሲኦል እየሆነበት መቷል። ከክልል ውጪም ያለው አማራ ላይ የዘር ጭፍጨፋው ቢቀጥልም የአማራ መሪዎች
ዝምታን መርጠዋል። ሞት እንደሚመጣ ይሰማል፤ እርምጃ ግን አይወስድም። ወረቀት አስተካክሎ መክተት
እንደተሳነው ሰው አይነት፤ አማራም ሁለቱንም አማርጮች፤ ወይ መሸሽ አለዚያም እራሱን መከላከል እንኳን ከብዶት
እንደበግ መታረጃ ካራው እየተሳለለት እያየና እየሰማ እንኳን ለመታረድ ቀኑን ይጠብቃል። በየቀኑም መታረዱን
ለምዶታል። ወከልኩት የሚለውም የአማራው ብልጽግና ፓርቲ ተብዬውም እጅግ ዘገምተኛ የሆነ፤ ለመንግስት
የተገዢነትና የባርበት ካዳበረውን የልማድ ሱሱ ሊላቀቅ ባለመቻሉ በተመሳሳይ የማህበረሰቡ አሉታዊ እምነቶችና
ባህሎች ተቋዳሽ የሆነ የችግሩ አካልም ሰለባም በመሆኑ ነገሮች የተወሳሰቡ መስለዋል። ከነሱ ወደተሻሉት ጥበበኞች
ሄደው እርዳታ ይጠይቃሉ ወይስ በባርነት ይቀጥላሉ የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚታረደውን የአማራ ደም ያስቆም
ወይም ይባስ ያስቀጥል ይሆናል። መለስ ዜናዊ ማሰብ የሚችሉ ብልሆችን ፈፅሞ አጠገቡ እንደማያስደርስ ያለፈ ታሪክ
ቢሆንም ይህን መረዳት የዛሬውን የፈነዳዳ የችግር ቁልል ለመገንዘብና መፍትሄ ለማምጣት እጅጉን ተቃሚ ነገር
Tribal Obsessions and Ethnic Divisions Might Lead Ethiopia To Cognitive Impairment ቅጥ ያጣው ጎሰኝነትና የዘር ክፍፍል ኢትዮጵያን ወደ ባሰ የአእምሮ ቀውስና የግንዛቤ እጦት ሊመራት ይችላል
Tribal Obsessions and Ethnic Divisions Might Lead Ethiopia To Cognitive Impairment ቅጥ ያጣው ጎሰኝነትና የዘር ክፍፍል ኢትዮጵያን ወደ ባሰ የአእምሮ ቀውስና የግንዛቤ እጦት ሊመራት ይችላል

More Related Content

Featured

2024 State of Marketing Report – by Hubspot
2024 State of Marketing Report – by Hubspot2024 State of Marketing Report – by Hubspot
2024 State of Marketing Report – by HubspotMarius Sescu
 
Everything You Need To Know About ChatGPT
Everything You Need To Know About ChatGPTEverything You Need To Know About ChatGPT
Everything You Need To Know About ChatGPTExpeed Software
 
Product Design Trends in 2024 | Teenage Engineerings
Product Design Trends in 2024 | Teenage EngineeringsProduct Design Trends in 2024 | Teenage Engineerings
Product Design Trends in 2024 | Teenage EngineeringsPixeldarts
 
How Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental Health
How Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental HealthHow Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental Health
How Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental HealthThinkNow
 
AI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdf
AI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdfAI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdf
AI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdfmarketingartwork
 
PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024
PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024
PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024Neil Kimberley
 
Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)
Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)
Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)contently
 
How to Prepare For a Successful Job Search for 2024
How to Prepare For a Successful Job Search for 2024How to Prepare For a Successful Job Search for 2024
How to Prepare For a Successful Job Search for 2024Albert Qian
 
Social Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie Insights
Social Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie InsightsSocial Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie Insights
Social Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie InsightsKurio // The Social Media Age(ncy)
 
Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024
Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024
Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024Search Engine Journal
 
5 Public speaking tips from TED - Visualized summary
5 Public speaking tips from TED - Visualized summary5 Public speaking tips from TED - Visualized summary
5 Public speaking tips from TED - Visualized summarySpeakerHub
 
ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd
ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd
ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd Clark Boyd
 
Getting into the tech field. what next
Getting into the tech field. what next Getting into the tech field. what next
Getting into the tech field. what next Tessa Mero
 
Google's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search Intent
Google's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search IntentGoogle's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search Intent
Google's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search IntentLily Ray
 
Time Management & Productivity - Best Practices
Time Management & Productivity -  Best PracticesTime Management & Productivity -  Best Practices
Time Management & Productivity - Best PracticesVit Horky
 
The six step guide to practical project management
The six step guide to practical project managementThe six step guide to practical project management
The six step guide to practical project managementMindGenius
 
Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...
Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...
Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...RachelPearson36
 

Featured (20)

2024 State of Marketing Report – by Hubspot
2024 State of Marketing Report – by Hubspot2024 State of Marketing Report – by Hubspot
2024 State of Marketing Report – by Hubspot
 
Everything You Need To Know About ChatGPT
Everything You Need To Know About ChatGPTEverything You Need To Know About ChatGPT
Everything You Need To Know About ChatGPT
 
Product Design Trends in 2024 | Teenage Engineerings
Product Design Trends in 2024 | Teenage EngineeringsProduct Design Trends in 2024 | Teenage Engineerings
Product Design Trends in 2024 | Teenage Engineerings
 
How Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental Health
How Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental HealthHow Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental Health
How Race, Age and Gender Shape Attitudes Towards Mental Health
 
AI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdf
AI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdfAI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdf
AI Trends in Creative Operations 2024 by Artwork Flow.pdf
 
Skeleton Culture Code
Skeleton Culture CodeSkeleton Culture Code
Skeleton Culture Code
 
PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024
PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024
PEPSICO Presentation to CAGNY Conference Feb 2024
 
Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)
Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)
Content Methodology: A Best Practices Report (Webinar)
 
How to Prepare For a Successful Job Search for 2024
How to Prepare For a Successful Job Search for 2024How to Prepare For a Successful Job Search for 2024
How to Prepare For a Successful Job Search for 2024
 
Social Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie Insights
Social Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie InsightsSocial Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie Insights
Social Media Marketing Trends 2024 // The Global Indie Insights
 
Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024
Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024
Trends In Paid Search: Navigating The Digital Landscape In 2024
 
5 Public speaking tips from TED - Visualized summary
5 Public speaking tips from TED - Visualized summary5 Public speaking tips from TED - Visualized summary
5 Public speaking tips from TED - Visualized summary
 
ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd
ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd
ChatGPT and the Future of Work - Clark Boyd
 
Getting into the tech field. what next
Getting into the tech field. what next Getting into the tech field. what next
Getting into the tech field. what next
 
Google's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search Intent
Google's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search IntentGoogle's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search Intent
Google's Just Not That Into You: Understanding Core Updates & Search Intent
 
How to have difficult conversations
How to have difficult conversations How to have difficult conversations
How to have difficult conversations
 
Introduction to Data Science
Introduction to Data ScienceIntroduction to Data Science
Introduction to Data Science
 
Time Management & Productivity - Best Practices
Time Management & Productivity -  Best PracticesTime Management & Productivity -  Best Practices
Time Management & Productivity - Best Practices
 
The six step guide to practical project management
The six step guide to practical project managementThe six step guide to practical project management
The six step guide to practical project management
 
Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...
Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...
Beginners Guide to TikTok for Search - Rachel Pearson - We are Tilt __ Bright...
 

Tribal Obsessions and Ethnic Divisions Might Lead Ethiopia To Cognitive Impairment ቅጥ ያጣው ጎሰኝነትና የዘር ክፍፍል ኢትዮጵያን ወደ ባሰ የአእምሮ ቀውስና የግንዛቤ እጦት ሊመራት ይችላል

  • 1. Samuel Lakew 1 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 Tribal Obsessions and Ethnic Divisions Might Lead Ethiopia To Cognitive Impairment ቅጥ ያጣው ጎሰኝነትና የዘር ክፍፍል ኢትዮጵያን ወደ ባሰ የአእምሮ ቀውስና የግንዛቤ እጦት ሊመራት ይችላል Samuel Tesema Lakew፡ (samuel.tesema@yahoo.com) University of Nottingham, United Kingdom, 5 January 2021 Websites and Social Links: Research Gate: https://www.researchgate.net/profile/Samuel_Lakew ORCID iD: https://orcid.org/0000-0001-7272-1470 Web of Science Researcher ID: P-2531-2017 መግቢያ ጥያቄ እንጠይቅ፤ ተገቢውን እና ትክክለኛውን ጥያቄ። ለጊዜው ማድረግ የምንችለው፤ ግን ደግሞ ሁልጊዜም ማድረግ የሚገባን ይህንኑ ነው። ተገቢውን ጥያቄ ሳያቋርጡ መጠየቅ። ለምሳሌ፣ ኢትዮጵያ ሃገራችን ለምን ከአለማችን ድሃ አገራት ተርታ ተሰለፈች? ለምን በሳይንስና ቴክኖሎጂ ካላደጉና ካልሰለጠኑ ቀዳሚዎቹ የአለማችን አገራት ጎራ ተገኘች? ለምን “ዜጎቿ” ለጋራ ጥቅም፣ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ እድገትና ብልጽግና መተባበር፣ መደማመጥና መግባባት የተሳነን የጥንታውያኑን የባቢሎንን ሰዎች አይነት ሆነን ተገኘን? ለምን ተፈጥሯዊ የሆነውን ክፉና ደጉን እንኳን መለየት ተሳነን? ዘርና ጎሳን መሰረት ያደረገውን የፖለቲካ ስርአት እንዴት ልንቀበል ቻልን? መሪዎቻችን ለምን አርቆ ማየት ተሳናቸው? የእኛስ እንደማህበረሰብ ከመጣው ገዢ ሁሉ ጋር በፍቅር የመክነፋችንንስ ነገር ምን እንበለው ይሆን?...ጥያቄው ይቀጥላል። ችግር የትዬለሌ በሆነበት ቦታና ሀገር ጥያቄውም የትየለሌ ቢሆን አይገርምም። ለመፍትሄ ፈላጊውና ነገር ግድ ለሚለው ለሃገር ተቆርቋሪው ለምን እና እንዴት ብሎ መጠየቁ ወደ መፍትሄው የሚያንደረድረው ድልድይ ሆኖ ያገለግለዋልና አብዝቶ ይጠይቅ። እኔም የዚህ ፅሁፍ ፀሃፊ፤ በሀገር ደረጃ እጅግ አሳሳቢ፣ ቀንደኛና ዋነኛ ተግዳሮት ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን መሰረታዊ ችግሮች ልናውቃቸው ይገባሉ ስል በበዕሬ ልከትባቸው ወሰንኩ። ሀገራችን አሁን ላለችበት የጨለማ ዘመን ውድቀት፣ የማህበረሰባችን የሞራል ልዕልናው መኮላሸትና መላሸቅ መንስኤው ምን እንደሆነ በቅደም ተከተል እያነሳሁ በማስረጃ እሞግታለሁ፤ እተቻለሁ። መፍትሄ የምለውንም እንደ አስፈላጊነቱ እጠቁማለሁ። ችግሮቻችንን የማለባበስና ሸፋፍኖ የማለፍ ልማድ ያለን ህዝቦች በመሆናችን እንደዚህ ላሉ ዝነኛ ላልሆኑ፤ ላልተለመዱና አከራካሪ (controversial) ለሆኑ ፅሁፎች ትኩረት ባንሰጥም፤ የማንሸራሽረው ዋናው ሃሳብ ግን የወደፊት እንደሃገርም ሆነ እንደግለሰብ የመቀጠል እድላችንን የሚወስን ብርቱ ጉዳይ በመሆኑ በእርጋታና በስክነት በማስተዋልም ጭምር እንዲነበብ ሲል ጸሃፊው በብዙ አክብሮት ከወዲሁ አንባቢያንን ያሳስባል። 0100010111
  • 2. Samuel Lakew 2 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 የድሮው እንዲህ ነበር አንዳንድ ጠቃሚ እውቀቶቻችን እና ልምዶቻችን ከአእምሯችን ጓዳ ተደብቀው ይኖራሉ። ብዙዎች ማሰብም ሆነ ማየት የማይፈልጓቸው የገሃዱ አለም እውነታዎች በመራራ ሃቅነታቸው ምክንያት ከሚከሰተው የስሜት ህመም ለመሸሽ እውነትን በመቃብር ቆልፈንባት እንኖራለን። እንደምናውቀው አባቶቻችን ብልሆች፣ ጥበበኞችና ጀግኖች እንደነበሩ የታሪክ መዛግብት ህያው ምስክሮችን አቁሞ ዛሬም ይነግረናል። የመሪነት ብቃታቸውም ሆነ ወኔያቸው ዛሬም ይደነቃል፤ ይዘከራል። መምራትና አገር ማስተባበር የተካኑበት ጥበባቸው ለመሆኑ ከእኛም አልፎ አለምም ጭምር ሳያቅማማ ይመሰክርላቸዋል። አለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ፤ የሰው ልጅም ይህቺን ምድር ከረገጠባት ቀን አንስቶ በግዛትና ድንበር ምክንያት፤ እንዲሁም በሌሎች ሰዋዊና ማህበረሰባዊ የፍላጎት ሽኩቻ መንስኤ እርስ በእርሱ ሲጋጭ ቆይቷል። የሰው ልጅ በህይወት ለመኖር በሚያደርገው ውጣውረድና ትንቅንቅ በዚህ መስመር ማለፉ ዛሬ ላገኘው የመኖር ህልውና ይህንን ማድረጉ ተገቢም የተለመደም ክስተት ነበር፤ አሁንም ድረስ። የቅርቦቹን የጣሊያንን 2 ወረራዎችን ግጭት ባንላቸውም እናስታውስና፤ ከነበረው የስልጣኔ ልዩነት፣የትጥቅ ዝግጅት አኳያ እንዴት የጣሊያንን ፋሺስታዊ ወራሪ ሃይል ልናሸንፍ ቻልን ብለን እራሳችንን ብንጠይቀው የምናገኘው ትርጉም ሰጪ የሆነ መልስ የጦር ትጥቅ ወይንም የተዋጊ ብዛት ሳይሆን አባቶቻችን ጥበበኞች ስለነበሩ ነው የሚል ይሆናል። ‘አባቶቻችን ብልህ ነበሩ’ ብዬ ስል የእውነትም እውቀትና ጥበብ የተሞሉ ነበሩ፤ ከፍተኛ የማገናዘብና ችሎታና ችግርንም በፍጥነት የመፍታት ተሰጥዖ የነበራቸው፤ የተጠቁና የተወረሩ ሆነው እያሉ እንኳን ሁኔታዎችን በመቀየር እራሳቸውንም ጭምር መስዋዕት እያደረጉ ኢትዮጵያን የታደጉ የአገር ኩራት የሆኑ ብልህ መሪዎች ነበሩ። አለም ከጻፈላቸው ታሪክ የምናነባቸው ገድሎቻቸው ይህንኑ ይናገራሉ፤ ይህንኑ ያሳያሉ [1]። የዚያ ዘመን በህይወትና ሞት መሃል ያለ ፍትግያ እና ግብግብ ቀላል ባለመሆኑ ስህተት ሰሪው ለርስህተቱ በነብሱ ዋጋ የሚከፍልበትና ሀገሩንም የሚያጣበት ከባድ ዘመን ነበር። ውድ አንባቢያን፤ እዚህ ጋር አስተውሉ። እነዚህ መሪዎች አባቶቻችን ቀልድና ፌዝ አያውቁም ነበር። የሚሰሩት ማንኛውም ጥቂት ምስል፡ አፄ ሚኒሊክ የመጀመሪያውን መኪና 1907 ዓ/ም ሲቀበሉና ለመንዳት ስልጠና ሲጀምሩ [2] የምትባል ስህተት እንዳልኩት መጨረሻ ወጤቷ ከሞት የከፋም እንደሆነ ጠንቅቀው ያውቁ ነበር። ሰው ሲሾሙና ወደ ሃላፊነት ቦታ ሲያመጡት ዝምድናውን አይተው አልነበረም፤ ከሆነም ብቃቱና ንቃቱም አብሮ ታይቶ፤ ለቦታው መመጠኑ ታሳቢ ሆኖ እንጂ። እንደዘመኑ ስልጣኔ መጠን ሙያተኞች፤ ነቃ ያሉ ቀልጣፎችና አሳቢዎች የተሻለ ቦታ
  • 3. Samuel Lakew 3 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ነበራቸው። ሁሉም እንደ ችሎታው፤ እንደማሰብ አቅሙ፣ ሙያውና ቅልጥፍናው ይሾማል፤ይሻራል። በወታደራዊ ሙያም ቢሆን ተቀጣሪው ብልህና ጤነኛ፤ ቀልጣፋ፣ እንዲሁም ጀግና፤ አገሩን እና ወገኑን የሚወድ መሆኑ ታይቶ ሊያገለግል ይቀጠር ነበር። ምናልባት ለዛም ይመስላል በዛ ዘመን፤ የቅኝ ወራሪዎች አፍሪቃን እንደቅርጫት ስጋ በተቀራመቷት ዘመን፤ ወታደር መሆን የተከበረ ስራ ተደርጎ በማህበረሰቡ ይቆጠር የነበረው። እነዚያ አይበገሬ የነበሩ፤ የአፍሪቃም ጭምር ኩራት የነበሩ መሪዎች አገር እንዲያድግ ህዝብም ስልጡን እንዲሆን በአቅማቸው ጥረዋል። የአጼ ሚኒሊክ ስልክና መኪና ለመጀመሪያ ጊዜ ማስገባት፤ ከቴክኖሎጂ ጋርም ማስተዋወቅ፤ የአጼ ቴዎድሮስም መድፍ ለመስራት ያደረጉት ጥረትና እውን ለማድረግም የሄዱበት እርቀት ሁሉ ይህን ለስልጣኔ የነበራቸውን ጉጉትና ፍላጎታቸውን አመላካች ነገሮች ናቸው [3]። ስልጣኔን መቀበልና መዘመን አገርን ከጠላት ለመጠበቅ ብርቱ መንገድ መሆኑን የተረዱ ነበሩ። በንጉሱ ጊዜም ቢሆን በርካታ የጭቆናና ብዝበዛ እንዲሁም ሌሎችም ችግሮች ተንሰራፍተው የነበሩ ቢሆንም፤ ማህበረሰቡ ለዘመናዊ ትምህርት ተነሳሽ እንዲሆን በጥቂቱም ቢሆን ይበረታታ ነበር። አልፎ አልፎም ከሲቪሉም ይሁን ከሚሊተሪው ዜጎች ተምረው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ በማለት በዘመኑ ሰለጠኑ ወደሚባሉት የምዕራቡ አለም እውቀት ቀስመው እንዲመለሱ ይደረግ እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ያወሳናል። የቀደሙትን የኢትዮጵያ ሃገራችን መሪዎች ትልቁ ጠንካራ ጎናቸው የሃገር ወዳድነታቸውና ለጠላት ያለመንበርከክ እንቢተኝነታቸው ነበር። ይህም የተለየና በአለም ያልታየ ወኔ እና ጀኝነት፣ እኛ ኢትዮጵያውያንን ብቸኛ በቅኝ ግዛት ያልተገዛን እና ያልተደፈርን እንድንሆን አድርጎናል። በዚህም ምክንያት በዘመናችን ሁሉ ጠንካራ ኢትዮጵያዊ ስሜት ያለው፤ ከሀገሩም አልፎ ለአፍሪካም ኩራት የነበረ የሃገር መከላከያ መገንባት ችለን እንደነበረ ታሪክ ያመላክታል። ዲሞክራሲና ዘር ተኮር ፖለቲካ “Democracy is the worst form of government – except for all the others that have been tried.” [Winston Churchill] አሁን ደሞ ጊዜያትን እና ሃሳቦችን ቦታና ጊዜ መድበን እንያቸው። አገራችን ኢትዮጵያ እንደ ሃገር መቆየትና መኖር መቻል ካለባት ወይንም እኛ ዜጎች መኖር አለብን ብለን ካመንን፤ እንደ ቀደሙት ጊዜያት ሁሉ ዘመኑ በሚፈቅደውን የአስተዳደር ስርአት ሳይሆን ለዘመኑ የሚመጥነውን መልካም የፖለቲካ ስርአት መገንባት ይገባናል ብዬ አምናለው። ይህም የሃገርን ታሪክ የሚያውቁና የሚያከብሩ፤ የማህበረሰቡን ባህልና እሴት ጠንቅቀው የተረዱ አዋቂዎችና ብልሆች የመሪነቱን ቦታ በየመስኩ በተዋረድ ሊይዙት፤ ሊመሩትና ሊያስተዳድሩት ይገባል ብዬ አጥብቄ እሞግታለሁ። ይህም ሃቅ ችግሮች ሳይከሰቱ ገና በግዜ ቢገባንና ብንተገብራቸው መልካም ነበር። አለዚያ ግን አንድ ቀን በባትሪም ፈልገንና ለምነን የማናገኛቸው የምጥ ጊዜያት መድረሱ አይቀርም። ዘር፣ ጎሳ፣ ብሄር፣ ቀለም እና ቋንቋ የምንላቸው ነገሮች ሁሉ ቦታ ሳይኖራቸው፤ ማሰብና ማገናዘብ የሚችሉ፤ በትምህርትም ብቃት የተደገፉ ሰዎችን በሁሉም የስራና የትምህርት መስክ ለራሳችንና የልጅ ልጆቻችን የወደፊት የመኖር ህልውና እንዲሁም ሁለገብ የሃገር ደህንነት ስንል እንደ ስልጡኖቹ ሀገራት ሁሉ እኛም ወደ መሪነት ሚና እንዲህ ያሉትን ልናመጣ ይገባል። በሃገራችን ሰዎች ችሎታቸው በሚመጥናቸው የስራ መስክ እና ደረጃ ላይ ሲያገለግሉ አይታዩም። ይህም መመዘኛው ዘርና ጎሳዊ ፖለቲካ በመሆኑ ነው። በአንድ ክልል ውስጥ ካለ አንድ ከክልሉ ከሚኖር የህክምና ዶክተር ይልቅ አንድ ልምድ የሌለው የግል ኮሌጅ ውስጥ ተየሰለጠነ የክልሉ ነዋሪ የነርስ ሙያ ምሩቅ ለቅጥር ተመራጭ መሆኑ አያጠያይቅም። በዚህም ሳቢያ ታሞ የሚድን አይኖርም። ወደ ክሊኒኩ የሚገባ እንጂ የሚወጣ ህይወት አይኖርም። የዘር ፖለቲካ መሠረቱ ደም ነው። ለሰው ልጅ ህይወት ክብር የለውም። ህይወትና እውቀት ግን አይነጣጠሉም። እውቀት ያለው፣ ጥበብንም የማይንቅ ውጣ ውረድን ተቋቁሞ በህይወት ይኖራል። እኔም የዘር ፖለቲካን የእውቀትና ጥበብ ጠላት ነው እለዋለሁ። ይህም እውቀትንና ጥበብን የመጥላት ልዩ ባህሪው ክቡር ለሆነውን የሰው ልጅ ቀንደኛ ጠላት እንዲሆን አድርጎታል። የዘር
  • 4. Samuel Lakew 4 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ፖለቲካ ልክ እንደ ቫይረስ ሁሉ ለቀጣይ ህልውናው የሚኖርበትና የሚባዛበት በህይወት ያለው አካል (host) ያስፈልገዋል። ይህም ሲሆን ብቻ እንደቫይረስ በፍጥነት ለመዛመት ይችላል። የሰውን ልጅም እንደ ሰው እንዲያስብ የተፈጠረለትን አእምሮ በቁጥጥር ስር በማዋልና በመቆጣጠር ከእንሰሶች በታች እንዲያስብና እንዲኖር ያስገድደዋል። በዚህም ምክንያት የጎሳ ፖለቲካ አራማጆች ተግባራቸውና ንግግራቸው አብሮ አይሄድም። የላሸቀ የሞራል ልዕልናቸውና የዘቀጠው ስብዕናቸው ለዚህ ጥሩ ማሳያ ሊሆን ይችላል። ሰው ምን ይለኛል ብሎ የሚወቅስ ህሊና የላቸውም። ማታለልና ማምታታት የዚህ አይነት ዘረኛ አገዛዝ ዋነኛ ስልት ነው። ሁሉም ሰው ለነሱ እቃቃ መጫወቻ ተሰርቶ የተሰጣቸው ስለሚመስላቸው፣ ህሊና ቢስ መሆናቸውን ላልተረዳ የዋህ ግለሰብ ለሰው ልጅ ያላቸው ጭካኔ እና ደመ ቀዝቃዛነት ቢመለከትም ምንጩ ምን እንደሆነ ግን አይገባውም። ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ በዘሩና በጎሳው እንዲሁም በቋንቋው ከፋፍሎ ለመመደብ፤ እንደ እንሰሳም ፓርክም አይነት አድርጎ በክልል ሸንሽኖ በማጎር፤ ከዚያም መልሶ ደሞ እስከፈለጉ ጊዜ ድረስ ብቻ የኢትዮጵያ አካል እንዲሆኑ ህግ በመደንገግ ለማታለል ወዘተ ድረስ መሄዱ ... ለዚህ የክፋት ስራ አመንጪና ፈጣሪነት ለመብቃት አንድ ሰው ምን ያህል ጥልቅ የሆነ ጨለምተኝነትና የአእምሮ መዛባት ቢከሰትበት ይሆን የዚህ ሰይጣናዊ የፈጠራ ባለቤት መሆን የቻለው በማለት በማዘንም ጭምር አስባለው። እንዲህ ስል እራሴን ጠየኩ፤ እኛ ኢትዮጵያውያን ምን አይነት ፍጹማዊ አስተዳደራዊ ስርአት ይሆን የምንፈልገው? የዲሞክራሲ አስተዳደር ስርአት ይሆን ወይስ እንደዚህ በዘር እና በመብት ነፃነት እያሳበበ ቀጥቅጦ የሚገዛ የዘር ፖለቲካ? ዲሞክራሲስ ቢሆን? ማነው ዲሞክራሲ ፍጹማዊ መንግስተ-ሰማይ መሰል ስርአትን (Utopia) ያመጣል ያለው? እንደ እኔ ዲሞክራሲ የሰው ልጆችን ደህንነት ዋስትና የሚያረጋግጥ መልካም የአገዛዝ ስርአት ነው ብዬ አላስብም። መራጮቹ መልካም ስብእና ካላቸውና የሚመርጡትን ሰው ጠንቅቀው ካወቁ፤ ምናልባት ዲሞክራሲ እዚህ ጋር ይሰራ ይሆናል። ምክንያቴንም እነሆኝ። ዲሞክራሲ ብዙሀኑ ትክክል ነው ብሎ የሚያምን እና ለድምጻቸውም ዋጋ የሚሰጥ ስርአት መሆኑን አውቃለሁ። ብዙሃኑ (majority) ትክክል ነው ብሎ በሚያምን አስተሳሰብ ላይ በመገንባቱም ብዙዎቻችን ለዲሞክራሲ ያለን አዎንታዊ ዝንባሌ ከዚሁ የተቀዳ ለመሆኑ አያከራክርም። ታሪክ ግን የሚነግረን ይህ እውነት አለመሆኑን ቢሆንስ እንቀበልና እራሳችንን እናስተካክል ይሆን? ብዙሃኑ ሂትለርን መርጦ አብሮት ብዙ ርቀት ተጉዟል። ላመኑበትም ሃሳብ የ 6 ሚሊዮኖችን የአይሁዶች ህይወት ለሂትለር ደስታ ቀጥፈው እንደ መስዋእት በደስታ አቅርበውለታል። የምለው ነገር ብዙሃኑ ሁሌም ትክክል የማይሆንበት አጋጣሚ በመኖሩ ዲሞክራሲም እዚህ ጋር ይወድቃል ባይ ነኝ። የፍልስፍናውም ሆነ የዲሞክራሲው አመንጪና ፈጣሪዎች ጥንታውያን ግሪኮች ሆነው ሳለ ፍልስፍናው ዲሞክራሲውን መቃወሙን መዘንጋት የለብንም። ለሃሳቤ መጎልበት የሶቅራጥስን ሙግት ልግዛውና ዲሞክራሲ ለብዙሃኑ ድምጹ እንዲሰማለት ስለሚያደርግ ብዙሃኑ ህዝብ በምርጫ ወቅት የሚወዳደረውን እጩ የህክምና ዶክተር ወይስ አፈ ቀላጤውን የጣፋጭ ምግብ ነጋዴ ይመርጣል? ምግብ ሻጩ ሰው በምግቡ ጥፍጥናውና በህዝቡ መሃይምነት ተጠቅሞ በማታለል ይመረጣል። ህዝቡም እውቀት አልባውን ምግብ ሻጭ መሪያቸው አደረጉ ማለት ነው። በዚህ ውስጥ ግን ጉዳቱን የሚያውቁት ጥቂቶች ናቸው። እናም ሶቅራጠስ ይህ ትክክል አይደለም ይለናል። የመራጭነት እድል ለማግኘት ሰዎች ምን እንደሚመርጡ፤ ተያያዥ ጥቅምና ጉዳቱንም አጥንተው ሲረዱ ነው ጥሩ መራጭ የሚሆኑት። መራጭነት የዜግነት ስጦታ ብቻ መሆን የለበትም። መራጩ ብዙሃን መሃይምና በቀላሉ የሚታለል በሆነበት የእኛ አይነት ማህበረሰብ ውስጥ ዲሞክራሲ ማለት የህጻን ልጅ ጨዋታ አይነት ነው። እንዲህ እንደ ጥንቷ ግሪክ ያለ ማህበረሰብ ክፉና ደጉን የሚለዩት ወይም እንበልና ወደ እውነተኛው ያልተጭበረበረ ዲሞክራሲ የሚመለሱት ለህይወት አስጊ የሆነ አደጋ ወይም ክስተት ሲመጣባቸው ብቻ የመሆኑ ክስተት ነገሩን ትንሽ
  • 5. Samuel Lakew 5 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 አስቂኝም ቢጤ ያደርገዋል። ለምሳሌ እንበና የመርከብ ጉዞ ስታደርግ በመርከቡ ያኩ ሰዎችን ሰብስባቸውና ለመርከቡ በትክክል መስራት እንዲረዳ ሰዎችን ምረጡ ብትላቸው ሙሉ በሙሉ የመርከብ ትምህርትና ልምድ ያለውን ብቻ ይመርጣሉ። ለምን? እዚህ ጋር የህይወት ጉዳይ በመሆኑ አይቀለድምና ችሎታና ብቃት ካላቸው ውጪ ምረጡም ተብለው ቢመከሩም ቢዘከሩም ፍንክች አያደርጉትም። ዲሞክራሲ ሁሌም እንዲህ ቢሆን እውቁ የግሪክ ፈላስፋም ሆነ ከዘመናት በኋላ እውነት እንደሆነ የተረዳሁት እኔም ዛሬ በደገፍነው ነበር። ታዲያ ይህን እውነታ ወስዶ በአገራችን ካለው ነገር ጋር አስተያይቶ ሁኔታውን ላጤነው የቅርቡቹ ሁለት ጦርነቶች ጥሩ ማሳያ ናቸው። በነዚህ ጦርነቶች ምክንያት የተባረሩ ፓይለቶችና እውቅ የጦር ጀነራሎች ተለምነው ወደ ስራቸው ሲመለሱ አይተናል። ታዲያ ለምን እውቀት አልባዎች እንዲመሩንና ለህይወትና ለወንበራቸው አስጊ እስኪመስላቸው ድረስ በመሃይምነታቸው እውርነት ሊያጠፉን እስኪደርሱ ድረስ ፈቀንላቸው? ለምን ታዲያ ለህይወታችን ዋጋ ከሰጠን መርከቧ በማእበል ወቅት ሆነ ያለ ማእበል በባለሙያዎች እንድትነዳ አናደርግም? ዲሞክራሲ በሁለት ምክንያቶች ውድቅ ሊሆን ወይም ላይሰራ ይችላል። አንደኛው በብዙሃኑ አማካኝ የግንዛቤ ብቃትና የእውቀት ልክ ሲወሰን ሌላው ደሞ የተመራጩ ግለሰብ ማንነትና ስብእና ላይ ይሆናል። የብዙሃኑ ውሳኔ እና የምርጫቸው ውጤት ምንነት እንዲሁ እንደ ብዙሃኑ ማንነት፣ ባህል፣ እምነት፣ የስልጣኔ መጠን ወዘተ ይወሰናል ማለት ነው። አንዳንዴ እነዚህ ‘ብዙሀን’ (majority) ተብለው የሚጠሩት የማህበረሰብ ክፍሎች ልክ በ 1930ዎቹና 40ዎቹ እንደነበሩት ብዝሀው የጀርመን ህዝብ እርኩስ ሃሳብ አንግበው ቢነሱስ? ለአናሳዎችስ ይህ ማለት እንደ አይሁዶች ይጨፍጨፉ ብሎ የይለፍ ፈቃድ እንደመስጠት አይሆንም? በሌላ መልኩ ደግሞ እንበልና ብዙሀኑ ህዝብ መሃይምና አማካኝ ዝቅተኛ የግንዛቤ ክህሎት (በተቀራራቢ ትርጉም ዝቅ ያለ IQ1 ያላቸው ሰዎች ለማለት ነው) ቢኖራቸው፤ እንዴት አውቀውና አገናዝበው ሀገር የመምራት ብቃት ያለውን፤ የማሰብና ማስተዋል ችሎታ፤ ሙያና ስብዕና ያለውን ተፈጥሯዊ መሪ አስተውለውና መርምርው መምረጥ ይችላሉ? ይህንንስ ጥያቄ የዲሞክራሲ መርህ ይመልሰዋል ወይ? በዚህ አጋጣሚ አንድ ነገር ለአንባቢዎቼ ከወዲሁ በጊዜ ግልጽ እንዲሆን ያህል፤ ለአሻሚና አላስፈላጊ ትርጉሞች አንባቢን እንዳይጋብዝ በማለት እንዲሁም የዚህ ጽሁፍም አንዱና ዋነኛ ማጠንጠኛ ሃሳብ በመሆኑ ይህ IQ1 ብለን ከምንለው ሃሳብ ጋር የተያያዘውን ነገር አጥርቼው ባልፍ ተገቢ ይሆናል ብዬ አስባለው። እንደሚታወቀው የማሰብ ችሎታና IQ ብለን ከምንጠራው የዚሁ መለኪያ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ንግግሮችና ውይይቶች ብዙ ሰዎች እንደማይወዱትና ምቾት እንደማይሰማቸው በሰፊው ይታወቃል። ቢሆንም እውነት ሲነገር የሚወራው ተቀናንሶና ተጨማምሮ ባለመሆኑ፤ እኔም ከእነዚህ የማህበረሰብ እምነቶችና ከስነልቦናዊ ተጽዕኗቸው ነጻ በመሆን እውነትን እንደሚፈል ሰው ይህንኑ እጽፋለው። እውነትን ለማግኘት በምናደርገው ጉዞ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በዚሁ በ IQ ዙርያ ልንወያይና ልንጽፍም ይገባል ስል እናንተንም እመክራለሁ፤ አበረታታለሁ። የሃይማኖት ሽፋን በማላበስና መሰል ነገሮችን በመጠቀም አላስፈላጊ ትልጓሜ ለመስጠት መሞከሩ አልያም ‘ለሃገር ክብር’ በሚል ተያያዥ እውነታን መደበቅ የማህበረሰባችንን ችግር ከማባባስ የዘለለ ምንም ፋይዳ አይኖረውምና እኔ በነጻነት እንደምጽፍ ሁሉ እናንተም ያለምንም ተጽዕኖ ነገር ግን በማስተዋል መወያየትና ሃሳብን ማንሸራሸሩ ክፋት የለውም ባይ ነኝ። 1 IQ ማለት Intelligence Quotient ለሚለው የእንግሊዘኛ ምህጻረ ቃል የቆመ ሲሆን፤ የፈተናውም ውጤት የአንድን ሰው ተፈጥሮሯዊ አዕምሯዊ ችሎታና እምቅ ክህሎት ለመለካት እንደመሳሪያ የሚያገለግል ነገር ነው። የግለሰቡ ተፈጥሯዊ አስተሳሰብ ፣ አመክንዮ አሰጣጥ እና ችግር አፈታት የመሳሰሉ የግንዛቤ ችሎታዎችን ለማንፀባረቅ ይጠቅማል።
  • 6. Samuel Lakew 6 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 የሃገራችን (የኢትዮጵያ) አብዛኛው ህዝብ ወይንም ማህበረሰብ በእኔ እምነት፤ ግን ደግሞ ምክንያቱ ሙሉ በሙሉ ባልገባኝ ሁኔታ ነገሮችን የማሰብና የማገናዘብ ብቃቱ እጅግ ዝቅ ያለ እንደሆነ ተገንዝቤያለሁ። ምንም እንኳን ይህ ጉዳይ ወይንም ችግር በመላው የአገሪቱ ክፍል የምናየውና የምንረዳው ነገር ቢሆንም፤ ብዙዎች ጉዳዩን ማየት የምንችል ሰዎች ግን ማመን አንፈልግም። ችግሩን እንደመመርመርና መፍትሄ ካለውም አጥንቶ መፍትሄ እንደመፈለግ፤ ምሁሮቻችን ግን እነሱም በክህደት ውስጥ ገብተው ሁሉም ሰላም እንደሆነ አድርገው ችላ ብለውታል። በቂና አሳማኝ በሆነ መልኩ ባይሆንም የውጪ ጥናቶችም ቢሆኑ ይህን ሃሳብ ከአንዴም ሁለቴ በማረጋገጣቸውና የኢትዮጵያን አማካኝ IQ መጠን በቁጥር 63 እና 67 በማለት ከሌሎች የአለም አገራት ዝርዝር ውጤት ውስጥ አካተው መጻፋቸው ብዙ ቁጣ ቀስቅሶ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው። ነገር ግን ትዕግስት አግኝቶ ነገሩን ላስተዋለው ሰው የነበረው ሁሉ ቁጣና ስድብ፤ ምክንያታዊነት የጎደለው ክርክርና ማብራሪያዎቹ በራሳቸው የኢንተርኔት መረጃው መሰብሰብና ማየት ለቻለ ሰው አንዱ የውጤቱን ትክክለኛነት ወይም ተቀራራቢነት ማሳያ ሆኖ ያገለግለዋል ብዬ አምናለው። በግልጽ ለመናገር ያህል፤ ህዝባችን ለማሰብ፤ ለማገናዘብና ነገሮችን ለመመርመር የሚደክመውና የሚዝል ህዝብ ነው ብዬ ብል ማጋነን አይሆንብኝም። እጅግ ብዙ የሚባለው የኢትዮጵያ ህዝብ ከእቅድ ይልቅ በደመነብስ መመራትን፤ ያለምክንያት መወሰንና መተግበርን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ነው። ከዚሁ ማህበረሰብ የወጡ መሪዎችም ያለምክንያት እረግጠውና ጨቁነው ሲመሩት ሰጥ ለበጥ ብሎ ይገዛል። ሲገድሉትም በዝምታ ይገደላል። ይህም በሌሎች ሰዎች ‘ትዕግስትና ቻይነት’ እየተባለ የማሳሳቻ ታርጋ ይለጠፍበታል። እውነታው ግን ያለማጋነን ለዚህ ህዝብ መንግስት ማለት ትርጓሜው አምላክ እንደማለት ያለ ነው። ‘በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ’ እንዲሉ፤ ከዝቅተኛ ንቃተህሊናና የማገናዘብ ችሎታ ላይ መሃይምነት ተጨምሮበት፤ አሁን አገራችን ያለችበትን አጣብቂኝ ሁኔታ ስናስበው ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመቱ ብዙ ምርምር የሚጠይቀን ጉዳይ አይሆንም። የማህበረሰባችን ‘ዲሞክራሲያዊ ስራትን’ አስፋኝ ይሆናል የተባለው ብዙሃን (majority) ምድቡ የትኛው ጋር ነው? ያልተማረውና በደመነብስ የሰማውን ሁሉ አምኖ በግምት የሚመርጠውን ወይስ እንደ የአዶልፍ ሂትለር ጀርመን ክፉ ሃስብ ተጠናውቶት በወደፊቷ ኢትዮጵያ የምናባዊ ስዕሉ ወስጥ ከአንድ ብሄር በስተቀር የሌላውን ኢትዮጵያዊ መኖር የማይታየው (tyranny of the majority2 )? ወይስ ሁለቱም? Professor Jordan Peterson “የማህበረሰብ ህልውና በሴቶች እጅ ነው” ከሁለት አመታት በፊት የአለማችን ምርጥ የስነ ልቦና ተመራማሪ በሆነው እውቁ በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲው ፕሮፌሰር ጆርዳን ፒተርሰን የሚተላለፍ ፐብሊክ ሌክቸር ላይ አንድ እንዳስብበት ያደረገኝን አከራካሪ ሃሳብ ሲናገር አዳመጥኩ። ነገሩ ባጭሩ እንዲህ ነው። አንድ ወጣት ሰው ፖስታ ውስጥ ወረቀቶችን በልኩ አጣጥፎ ለማስገባት ሲታገል ይህ ፕሮፌሰር ይመለከተዋል። 30 ደቂቃ አለፈ፣ ወጣቱ ሰው ግን አስተካክሎና አጣጥፎ ማስገባት አልቻለም። በኋላም ሊረዳው በመወሰን የተለያዩ ወረቀቶችና ፎቶዎች እንዴት ፎቶው ሳይታጠፍ ማስገባት እንደሚችል 30 ሰአታት የፈጀ ስልጠና ሰጠው። ይህን ሰው አዲስ ሙያ ማስተማር ከባድ ነበር። ሌላ አንድ ተራ ነገር ለመማርም እንዲሁ 6 ወርና አመት ይፈጂበታል እንደማለት ነው። ይህን ሰው ስራ የሚቀጥረው የለም። የነጻ አገልግሎት በመስጠት (volunteering) ነበር የሚያገለግለው። በኋላ ግን እሱንም ቢሆን ሊቀጥል አልቻለም። የሚያደርገው መስራት 2 Tyranny of The Majority (Tyranny of The Masses) is an inherent weakness to majority rule in which the majority of an electorate pursues exclusively its own objectives at the expense of those of the minority factions. This results in oppression of minority groups comparable to that of a tyrant or despot. [17]
  • 7. Samuel Lakew 7 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ሳይሆን እንዴት እንደሚሰራ ሰዎችን እርዳታ በመጠየቅ የስራውን ክፍለ ጊዜ ማቃጠል ነበር። በኋላም ቀጣሪዎቹ የሰለቻቸው ይመስላል ከነጻ አገልግሎት ስራውም አባረሩት። ፕሮፌሰር ፒተርሰን እንዳለው ይህ ሰው በጣም ዝቅተኛ (ከ 80 በታች IQ) እንዳለውና፤ ነገር ግን ከውጪው ሲታይ እንደማንኛውም ጤነኛ ሰው እንደሆነና ላዩን አይቶ የዚህን ሰው ችግርና ሁኔታውን ለመገመትም እንደሚከብድ ገልጿል [4]። ፕሮፌሰር ፒተርሰንን እንደሌሎች በዘርፉ እንደተሰማሩ ተራ የስነልቦና ምሁራን አድርጌ አላየውም። ምንም እንኳን ሁሉንም አመለካከቱን እና ስራዎቹን እጋራለው ባልልም፤ እጅግ ምጡቅ ተመራማሪና መምህር በመሆኑ አድናቂው እንድሆን አድርጎኛል። እውነታን አጣቅሶ በማስረጃ አዋዝቶ ነብስ ዘርቶበት የሚሞግተውን ሃሳብ የሚያቀርብ፤ ለሰው ልጆች ጠቃሚ የሆነ ጥሩ ችግር ፈቺ ተመራማሪና መምህርም ነው። በአለም ላይ ልናገኛቸው ከምንችላቸው ጥቂት የዘርፉ ምሁራን ውስጥ አንዱና ቀዳሚው ሰው ነው ብልም ማጋነን አይሆንም። ይህን የምለው የዚህን ግለሰብ ለሰው ልጅ ያለውን ጥቅምና ዋጋ ግምት ውስጥ በመክተት ነው። ፕሮፌሰሩ በዚህ ሌክቸር ወቅት ታዲያ ትኩረት ሰጥቶ በዋናነት ይናገር የነበረው የማህበረሰቡ ግማሽ አካል ስለሆኑ የሴቶች እህቶቻችንን ባህሪ ሲሆን፤ ይህም እንዴት አድርጎ ማህበረሰብን እየቀረጸና አየመራ እንዳለ፤ እንደነበረም የሚያብራራ ነበር። ለመሆኑ ሴቶች አብሮ መኖርን ሲያስቡ ምን አይነት ወንድን ነው የሚያስቡት ወይም የሚማርካቸው/የሚስባቸው? ነገሩ ሰፊና ፕሮፌሰሩ የሰራውንም ምርምር የሚያካትት በመሆኑ እኔም እዚህ ልጽፈው ቦታው ባይሆንም፤ እጅግ ጠቃሚ የሆነውን ክፍል ብቻ ለሃሳቤ ማጠናከሪያና አስረጂ ሆኖ ስላገኘሁት በአጭሩ ሃሳቡን ጨምቄ እንደሚከተለው ፅፌዋለሁ። Jordan Peterson, a Canadian psychology professor (From his reddit blog) ዘመኑ የእውቀትና የመረጃ ነው። በዚህ ዘመን በምእራቡ አለም ትንሽ የተሻለ IQ ያለው ግለሰብ ባብዛኛው ቢያንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ይኖረዋልና በንፅፅር ሲታይ ከሌላው የተሻለ አመታዊ ገቢና የኑሮ ደረጃ አለው። ቀጣሪ ካምፓኒዎችም የተሻለ ልምድና የትምህርት ደረጃ ስለሚጠይቁ፤ ቃለመጠይቃቸውም ቀሪውን መልስ ስለሚመልስላቸው፤ ዝቅተኛ IQ ያለው ሰው የተሻሉ የስራ ቦታዎችን የማግኘት እድሉ የመነመነ በመሆኑ የአቅሙን በመፈለግ የሚመጥነው የስራ አይነት ላይ መሰማራቱ፤ ለዚያም የሚመጥን የሙያ ስልጠና ወስዶ መዘጋጀቱ የተለመደና ማህበረሰቡም የተቀበለው ጉዳይ ነው። በሌላ አገላለጽ፤ አንድ ሰው በምዕራቡ አለም የአኗኗር ዘዬ ስኬታማ ከሆነ የተሻለ የማሰብና የማገናዘብ ብቃት አለው፤ የተሻለ IQ አለው ወደ ሚለው ድምዳሜ ያደርሰናል። ይህን ይዘን ወደ አፍሪቃና በተለይ ወደ ኢትዮጵያ ስንመለስ የሰዎችን የመቀጠር ሁኔታና በአጠቃላይ የስኬታቸውን መነሻ ስንመረምር ነገሩ ፈጽሞ ሌላ ታሪክ ህኖ እናገኘዋለን። በአገራችን ለ 30 አመታት ስር ሰዶ በተንሰራፋው ዘር፣ ቋንቋ Jordan Bernt Peterson (born 12 June 1962) is a Canadian clinical psychologist and a professor of psychology at the University of Toronto. He began to receive widespread attention in the late 2010s for his views on cultural and political issues. Born and raised in Alberta, Peterson obtained bachelor's degrees in political science and psychology from the University of Alberta and a PhD in clinical psychology from McGill University. After teaching and research at Harvard University, he returned to Canada in 1998 to join the faculty of psychology at the University of Toronto. In 1999, he published his first book, Maps of Meaning: The Architecture of Belief, which became the basis for many of his subsequent lectures. The book combined information from psychology, mythology, religion, literature, philosophy, and neuroscience to analyse systems of belief and meaning.
  • 8. Samuel Lakew 8 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 እና ክልል ተኮር የሆነው የሃሰት ፌዴራሊዝም (Pseudo Federalism3 ) ፤ አብዛኛው አቅምን የሚጠይቁ ለሀገር ጠቃሚ የሆኑ የስራ መደቦች ግለሰቡ በዘሩና በቋንቋው እንዲሁም ለገዥው መደብ በተግባር በሚያሳየው ታማኝነትና ተገዥነት የሚሰጠው ስጦታና ችሮታ እንጂ ተምሮ ባገኘው እውቀትም ሆነ ልምድ አዳብሮ የተሻለ በመሆኑ ተገብቶት የሚቀጠርበት አይደለም። ታዲያ አሁንም ወደ መዕራባውያኑ ባህል ስንመለስ አንዲትን ሴት ልጅ የሚማርካት ነገር የሰውየው ሃብታም መሆን ሳይሆን ስኬታማና ዲሲፕሊኑ ሲሆን ይህም የተሻለና ለዚህ እንዲበቃ ያደረገው የኝዛቤ ክህሎት ወይም IQ እንዳለው ስለሚያመለክታትና ስለሚጠቁማት ነው ብሎ ያምናል፤ ፕሮፍፌሰር ፒተርሰን። በተቃራኒው በኛ ሀገር የተሻለ ስኬት ላይ የሚገኙ ሰዎች በሴት እህቶቻችን ብቻ ሳይሆን በማናችንም ቢሆን ቀድሞ ወደ አእምሯችን የሚመጣው ሃሳብ የግለሰቡ የመንግስት ሰው የመሆን እድሉ ከፍተኛ መሆኑ ነው። እንበልና ትንሽ ወደ ኋላ አንድ ሺህ አመት ያህል ተጉዘን ብንመለከት፤ የዚያ ዘመን ሴቶች የሚስባቸው ወይንም የሚማርካቸው ወንድ ምን አይነት ነገሮችን ያሟላ ይሆን ብለን እንጠይቅ። የምናገነውም መልስ እንደዚህኛው ዘመን ትልቅ የ IQ መጠን ያለው ሰው ሳይሆን እጅግ ትልቅ ተክለ ሰውነት ያለው እንደነበር ከአለም የታሪክ መዛግብት እንረዳለን። የግሪኮችን አፈታሪክ እንኳን ትተን የእኛን ሃይማኖታዊ የታሪክ አዘል ማስረጃዎችን ብንወስድ እንኳን፤ በመጽሃፈ ሄኖክ [5] እና መጽሃፍ ቅዱስ [6] ፤ የሰው ልጅ ሴቶች ልጆች ከተራ ሰው ይልቅ ለየት ላሉ ሰዎች ወይም መለኮታዊ ለመሰሏቸው ፍጡሮች የመሳብ አዝማሚያ እንደነበራቸው ሳይጠቁሙ አላለፉም። እዚህ ጋር ይህ ተወራራሽ የሆነ የሰው ልጅ ስነልቦናዊ ተፅዕኖ በኛም አገር አብዛኞቹ እህቶቻችን ዘንድ ለጸጉረ ልውጦች፣ ለጣሊያን ወይም ለኩባ ክልሶች እንደሚማረኩላቸው አይነት ባለ መልኩ አሁንም ድረስ እንደሚንጸባረቅ ልብ ይሏል። ታዲያ የድሮው ዘመን ሴቶች ለምን ምርጫቸው ይህ ሆነ ለሚለው ጥያቄ ውሃ የሚያነሳልን ልናገኘው የምንችለው ሚዛን ደፊ መልስ የዘመኑ ውድ እና ተፈላጊ ነገር ደህንነት (safety/security) ስለነበር ነው። በአጭሩ ቀጥታ ስንናገረው አንዲት ሴት የመኖር ህልውናዋን ለማረጋገጥ ከጠላት የሚጠብቃት ጉልበተኛና ጡንቸኛ ወንድ ነበር የሚያስፈልጋት ማለት ነው። ግዙፍ የሆነ ጡንቸኛ ሰው በዘመኑ የተሻለ የኢኮኖሚ ዋስትናም ስለሚኖረው የሴቷ እረጅም እድሜ የመኖር እድሏ (probability of survival) ይጨምራል። ትልቅ ጡንቻ በድሮ ዘመን፤ ትልቅ አእምሮ/የማሰብ አቅም ደግሞ በዚህ ዘመን ማለት ነው። ይህን ስል የዝግመተ ህይወት (Theory of Evolution)4 ሰባኪም ሆነ ተቀባይ ሆኜ አይደለም። የዚሁ መስክ ተመራማሪዎች ለራሳቸው እንዲመች አድርገው በሳይንስ ስም የተረኩትን ተረት ባልቀበልም አንዳንድ እውነት የሆኑ አሳማኝ ማስረጃ ያላቸውን፤ በዚህም ዘመን በአይን የሚታዩና የሚጨበጡ ከላይ እንደጠቀስኩት ያሉ ጽንሰ ሃሳቦችን ግን እጋራቸዋለሁ። ለምሳሌ ያህል ከእነዚህ ውስጥ የቻርለስ ዳርዊንን “ብቃት ያለው ይኖራል” (Survival of the Fittest) ፅንሰ ሃሳቡን ብንወስድ መሉ በሙሉ ባይሰራም፤ ሌሎችም የሰውን የመኖር እድል የሚወስኑ ጉዳዮች ያሉ ቢሆንም፤ ከማነሳው ሃሳብ ጋር አብሮ የሚሄድ ተፅዕኖ ፈጣሪ ገዢ 3 የውሸት ፌዴራሊዝም (Pseudo Federalism) ማለት ከተለመደው ወጣ ያለና በሌላው አለም የፌዴራሊዝም ባህሪያት ያፈነገጠ፤ ለይስሙላ ብቻ በህገ መንግስት ላይ ይስፈር እንጂ የተለያዩ ክልሎች ወይንም ፓርቲዎችን በራሳቸው የመወሰን እድል የማይሰጥ፤ ነፃና ዲሞክራሲያዊ ምርጫን ከወረቀት በቀር ይርማይተገብር፤ ከዚያም አልፎ በእኛ አገር በተለይ አንደሚታየው ለአገር ህልውናና አንድነት ፀር የሆነ ክልሎችን እስከመንገንጠል የሚያደርስ እንደ አንቀፅ 39 አይነት ያለና ዜጎችን ከክልላቸው ውጪ የመኖር መብት የሚነፍግ እንዲሁም ሌሎች አደገኛ የሆኑ ህግና ደምበችን የያዘ በመሆኑ ነው። 4 In the 1850s, Charles Darwin wrote an influential and controversial book called The Origin of Species. In it, he proposed that species evolve (or, as he put it, undergo "descent with modification"), and that all living things can trace their descent to a common ancestor. Darwin also suggested a mechanism for evolution: natural selection, in which heritable traits that help organisms survive and reproduce become more common in a population over time [7].
  • 9. Samuel Lakew 9 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ሃሳብ ነው ብዬ ግን አምናለሁ። በድሮ ጊዜ ብቃት ማለት ትልቅ ጡንቻ ወይም ጉልበት ያለው ማለት ነበር፤ አሁን ደሞ የአእምሮ የማሰብ ብቃት (Intelligence) ሆኖ እናገኘዋለን። ታዲያ ይህ ማለት በዚያ ዘመን የሰው ንቃተ ህሊና ዋጋ የለውም ማለት እንዳልሆነ ይስተዋል እላለሁ። ሳልጠቁመው የማላልፈው ነገር፤ የሰውን ንቃተ ህሊና ወይም የማገናዘብ ብቃት ለመግለጽ በተደጋጋሚ የተለያዩ ገላጭ ቃላትን ጨመሬ ብጠቀምም፤ የሰውን ልጅ ንቃተ ህሊና በአንድ ፈተናና የይወት ተሞክሮ ታይቶ እንዲህ ነው ለማለት ስለሚከብደኝ እኔም አንባቢዬን እንዳላሳስት አድማሱን ለማስፋት በዚህ መልኩ ለመግለጽ ወሰንኩ። ጊዜና ሁኔታዎች እየተቀያየሩ ቢመጡም የዚህ ዘመን ሴቶች እህቶቻችንም ከቀድሞዎቹ የተለዩ ናቸው ማለት አይደልም። ሁሌም ጥያቄው በመኖርና ባለመኖር መካከል የሚንሸራሸር ሆኖ እናገኘዋለን። ሁልጊዜም የማይቀየሩ ቁልፍ የሆኑ የህይወታቸው መሪ ጥያቄዎች ዘላቂ ደህንነት እና የኢኮኖሚ ዋስትና (Sustainable peace and Security and Stable Economical Status) ናቸው። እግረመንገዳችንን የምናስተውለው ነገር ታዲያ ይህ ባህል ሲሆንና ሲደጋገም ይሄው ጠንካራ የሰው ባህሪያችን ተሸካሚው የዘር ሃብል (genetic trait) ለመጪውም ዘመን የመኖር እድል ያገኛል ማለት ነው። የሚገርመው ነገር ታዲያ በተመሳሳይ ጊዜ ወይም ዘመን ግን ደግሞ በቦታ ልዩነት ይህንን የሰው ልጅ ባህሪ ወይንም የማህበረሰብ ባህል በተቃራኒው ማየታችን ነው። ለምሳሌ ወደ እኛ አገር ስንመለስ፤ ሴቶች ምርጫቸው በኢኮኖሚ አቋሙ የተሻለ ሰው ነው። ምንም እንኳን ግለሰቡ ሰርቶ ባያመጣውም አብሮት የሚገዛው መንግስት እስካለ ሃብታም ሆኖ እንደሚቆይ ታስባለች። ሃብታምና ደህንነቷን ጠባቂ ሰው ነው ምርጫዋ። የሰውየው የማሰብ ብቃት፣ የሞራሉ ልእልና ጉዳይ ወይንም ስብእና እንዲሁም አካላዊ የሆኑ ነግሮች ሁሉ እንደመምረጫ አይታዩም። ምክያቱ ደግም ግልጽ ነው፤ የኢኮኖሚያዊና የደህንነት ዋስትናን አመላካች እንዳልሆኑ ታውቃለችና ነው። ስለዚህ በእኛ አገር አንድ ወንድ ወጣት ሴቶችን ለመሳብና ቤተሰብ መስርቶ ኑሮ መጀመር ካለበት፤ ሃብታምና ደህንነቷን አስጠባቂ ወደመሆን እራሱን በሂደት መቀየር ግዴታው ነው እንደማለት ነው። ምክንያቱም አጠቃላይ ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ማህበረሰቡ በአመዛኙ ዋጋ የሚሰጠው ሃሳብና እምነት ይሄው የኢኮኖሚና የደህንነት ጉዳይ ስለሆነ ነው። የብዙሃን አምባገነንነትና አናሳ ንቃተህሊና (Tyranny of The Majority & Lower Intelligence) የአናሳዎች የአካልና ስነልቦና ሰለባ መሆን (Mind Control & Genocide) ጠ/ሚ አብይ አህመድ የዚህን ማህበረሰብ ባህሪ አጥንተው የመጡ ሰው ይመስላሉ (ፓርቲአቸውን ብልጽግና እስከማለት መድረሳቸውን ስናይ ማለቴ ነው)። ምንም እንኩዋን ጉዟችን የደም ጎርፍ የበዛበት ሸካራ መንገድ ቢሆንም፤ ማህበረሰቡ ግን የንጹሃን አማራ ብሄር ተወላጆች በብሄራቸው ምክንያት በተገኙበት መታረድ ነገር ለመጪው ብልጽግናቸው እንደሚከፈል ጥቂት መስዋዕትነት በማድረግ ቀለል አድርገው ሲመለከቱ አይቶ ለተረዳ ሰው ይህ ነገር (እንደ Tarrany of the majority አይነት ማለት ነው) በማህበረሰቡም ሆነ ተቃዋሚ ፓርቲ በሚባሉት ዘንድ ስር ሰዶ ያለ ግዙፍ ችግር መሆኑን ይረዳል። ታዲያ እንዲህ ያሉ የማህበረሰብን ባህሪ ቀያሪ ሃሳቦች 27 አመት እንደሆነው ሁሉ አሁንም ድረስ በባሰ ሁኔታ በማህበረሰቡ ውስጥ ለማስረጽ ወይንም ጭንቅላታቸውን እንደ ኮምፒውተር ፕሮግራም ለማድረግ (Mind Control5 ) የአብይ አህመድ የአገዛዝ ስርአት ሚዲያን በበላይነት 5 Mind Control (also known as, Brainwashing, menticide, coercive persuasion, thought control, thought reform, and re-education) is the concept that the human mind can be altered or controlled by certain psychological techniques. Brainwashing is said to reduce its subjects' ability to think critically or
  • 10. Samuel Lakew 10 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 በሞኖፖሊ በመቆጣጠር፤ የኢንፎርሜሽን ፍሰቱን በመገደብ ከራሱ ስርጭት በስተቀር ሰዎች ሌሎችን አማራጭ ነጻ ሚዲያዎችን እንዳይሰሙ ይህንኑ እነ አዶልፍ ሂትለር የተገበሩትን ፀረ-ሰው ድርጊት በተለያየ መንገድ እየተገበረው ይገኛል። ልክ ህወሃት ያደርገው እንደነበረ ሁሉ፤ ይህም አገዛዝ መጻህፍትን በመጻፍና በማስጻፍ፣የመዝናኛ ድርራማዎችና ፊልሞችን ሁሉ ይዘት በመቆጣጠርና በመጠቀም የሚፈልገውን የMind Control ይለፍ ቃላቶችንና መልእክቶች ሰለቸኝ ደከመኝ ሳይል እየተገበረው ይገኛል። ይህንንም ‘ድምጽ የለሹ የሰው ልጅን መግደያ መሳሪያ’ ብቻ በማለት እገልጸዋለው። ታዲያ ይሄ ሃሳብ ሲሰርጽ ልምድ ከዛም ቆይቶ እንደባህል ይሆናል፤ ይቆጠራል። ከዚያም መንግስትም ሆነ ከያንያን ተወቃሽ ተነቃሽም ሳይሆኑ ፊልሙም ሆነ ልብ ወለዱ ‘የገሃዱ አለም ነፀብራቅ ናቸው’ መባሉ ይቀጥላል። እውነትም ልክ ነው፤ አሁን የማህበረሰብ ባህልና ልምድ ሆኗልና፤ እነሱ ዲዛይን ያደረጉት ሰው ሰራሽ የማህበረሰብ ባህሪ (behaviural modification6 ) ለውጥ ልምዱ፣ ባህሉና እሴቱ ሆነው ይቀራሉና። እውነቱን ከሚያውቀው በቀር ውሸቱ ‘እውነት’ ሆኖ እንደተፈበረከ ማን ያውቃል፤ማንስ ይረዳል? ለመሆኑ እውነትስ ምንድነው? እውነትንስ ማን ያውቃታል? ማንስ እውነተኛ ሆኖ ይናገራታል? የፕሮፌሰር ፒተርሰንን ሃሳብ ወስጄ ያገራችንንም ሁኔታ ሳጤነው መሉ በሙሉ ባይሆንም አብዛኛው ተምሪያለሁ የሚል የአገራችን ወንድ ሰው ለአብዛኞች የኢትዮጵያ ሴቶች እህቶቻችን ለባልነት ተመራጭ አይሆኑም ማለት ነው ወደሚል አስቂኝ መሳይ መደምደሚያ ልድረስ ይሆን? አስቂኝም አሳዛኝም እውነታ! በዚህ (በኢትዮጵያ) ማህበረሰብ ውበትና ቁመና፣ ወንዳወንድነትና እውቅት፤ እንዲሁም ተፈጥሯዊ ክህሎትም ሆነ የማገናዘብ ችሎታ ወዘተ የምንላቸው ነገሮች ሁሉ ከቶውንም ቦታ እያጡ የመጡበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። የተማረ እና ትልቅ IQ ያለው ቢገኝ እንኳን አገሪቷ ለእንደዚህ አይነት ሰዎች ቦታ ስለሌላትና ምቾት ልትሰጥ የማትችል በመሆኗ ስኬታማ ደልዳላ ህይወት ለነሱ አይታሰብም፤ ሃብትና ንብረት አያፈሩም ፤ሰርተው አይበለጽጉም። የማህበረሰቡ ሴቶችም በኢኮኖሚያዊና የወደፊት የደህንነት ዋስትና ሊለግሷቸው የሚችሉ ግለሰቦች ፊታቸውን ያቀናሉ ማለት ነው። እንግዲህ እዚህ ላይ ከተባለው ሁሉ ደግሞ ተጨማሪ መረሳት የሌለበት ማህበረሰቡ በዘርና በጎሳ መከፋፈሉን፤ በዘር ማሰቡን፤ ማህበራዊ ግኑኝነቶች ጋብቻን ጨምሮ ሌሎችም ከዘርና ጎሳ እሳቤ ጋር መዛመዳቸውና መሰናሰላቸው የኢትዮጵያን ማህበረሰባዊ ቀውስ ከምናስበው በላይ የትዬለሌ ያደርሰዋል። ይህ ደግሞ እንደሚደጋገም የህይወት ኡደት (vicious circle) አሁንም ጭምር ሲቀጥል በመቆየቱ፤ የማህበረሰባችን ስሪት ማያያዣ መልካም እሴቶችና ባህል ቀስ በቀስ እንደክር እየተመዘዘ በመሄዱ የማህበረሰቡ የራሱም ሆነ የአገርን ውድቀት እጅግ እያፋጠነው ይገኛል ብዬ አምናለው። ላይ ላዩን የማህበረሰባችንን ያስተሳሰብ ልቀት፤ እይታና እምነት በማየት አንዳንዶቻችን ከምዕራቡ አለም ምን ለየው ብለን እንል ይሆናል። ከላይ እንደጠቆምኩት ምንም እንኩዋን ገዢው መንግስት ወንጀለኛና በዜጎች ደም ችርቻሮ የሚተዳደር ነጋዴ መሆኑን ቢያውቁም፤ ወንዶችም ሆኑ ሴቶቹ ለፍላጎታቸው እና የመኖር ዋስትናቸው ሲሉ ለማንኛውም ሞራል የለሽ ተግባርና የዘቀጠ ስብእና ተገዢ ሆነው እናገኛቸዋለን። የማሰብ ችሎታው ዝቅተኝነት ከእውቀት መሳሳት ጋር ተደምሮ ለኢሞራላዊ ድርጊታቸው አስተዋፃዖ እያበረከተ ይገኛል። የዚህ ዝቅጠት ውጤት ለራስም ሆነ ለሌላው ሰው መጪውን አደጋ ሳያገናዝቡ በደመነብስ መኖርን አስከተለ። ይህ ከሌላው አለም የሚለየን፤ independently, [8] to allow the introduction of new, unwanted thoughts and ideas into their minds,[9] as well as to change their attitudes, values, and beliefs.[10] 6 Is also part of mind control, in fact it is the desired outcome of mind control or brainwashing. It is good to remember here the CIA mind control program after world war II known by a project code name ‘Project MKUltra (or MK-Ultra)’. [11]
  • 11. Samuel Lakew 11 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ታሪካችንም ከሚነግረን እንዲሁም የሃይማኖትና የስነምግባር ሰዎች የመሆናችን ትርክት ጋር አብሮ የማይሄድና የማይጣጣም፤ የገዘፈ ተቃርኖ ያለው ጉዳይ ሆኖ አግኝቸዋለሁ። ይህ የማህረሰቡ የባህልና ልምድ ፈጣን ለውጥ ታዲያ ለብዙ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ምሁራን እሳቤ ውስጥ ባለመግባቱ አልያም እየታወቀ በመካዱ ወይም እነሱም በማህበረሰቡና በአገራችን የቆሸሸ ዘርና ጎሳ ተኮር የውሸት የፌዴራሊዝም ፖለቲካዊ አመለካከት ሰለባ በመሆናቸው መፍትሄው ላይ እንዳይሰሩ ወይም መስራት እንዳይችሉ አድርጓቸዋል ብዬ አምናለሁ። ችግርን ማመን፤ ለይቶም ማወቅ (problem identification and acknowledgement) ለመፍትሄው ስኬት ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ መረሳት የሌለበት መሰረታዊ እውነታ ነው። ማህበረሰባችን የአንድን የአምነት ተቋም ይመስላል ብዬ አስባለሁ። ከገዢዎቹ የሚነገረውን ሁሉ እውነት ነው ብሎ የሚቀበል፤ ቃላቸውን እንደ እምነት ቅዱስ ቃል የሚቆጥር የእምነት ቤቱ ምዕመናንን ይመስላል። ገዥዎችም በመጡ ቁጥር፤ ልክ እንደ ታማኝና እውነተኛ አምልኮ ፈጻሚ ሰው ከመገዛትም አልፎ ያመልካቸዋል፤ እንደ አምላክም ቆጥሮ ይፈራቸዋል፤ እምነቱን እና ተስፋውን ሁሉ በነሱ ላይ ይጥላል፤ በህይወት የመቆየቱንም እድል በእጃቸው ያኖረዋል። ለደህንነቱ የሚከፈል ዋጋ ይመስል ታዲያ ማህበረሰቡ በውስጡ አቅፎ ለሚይዛቸውን ጥቂት ንቃተ ህሊናቸው የላቁና የጎለበቱ የማህበረሰቡ አንቂና ቀስቃሽ፤ የመብቱም ተሟጋቾችን አሳልፎ በመስጠት ቁስሉን እየላሰና በኋላም እየበላ እራሱን እንደሚጨርስ አይነት ጅብ በመሆን ለራሱም ለነሱም መጥፊያ መንስኤ ሆኗል። አንዳንዴ ደሞ ማህበረሰባችን እንደ ወታደርም መስሎ ይታየኛል። አድርግ የተባለውን የሚያደርግ፤ አታድርግ የተባለውንም ለምን ሳይል የማያደርግ። አስፈላጊም ሲሆን ገዢው መንግስት እንደ ኮምፒውተር በቀላሉ ፕሮግራም በማድረግ ጠላቴ የሚለውን የሚያጠቃበት አደገኛ መሳሪያውም ነው። በወታደር ቤትና ህግ ታዲያ ወታደሩ ‘ለምን’ እና ‘እንዴት’ ብሎ አይጠይቅምና፤ ይህም ማህበረሰብ እንደዛው ሆኖ በማግኘቴ ይሄን አልኩ። የሚጠባበቀው ከሰመመን የሚያነቃውን የይለፍ ቃል (ወይም pass word) ብቻ ይመስላል። አጨብጭብ ሲባል የሚያጨበጭብ፤ ዝፈን ወይም ጨፍር ሲባልም እንደተባለው የሚያደርግ ማንኛውንም ሶፍትዌር እንደሚቀበል ያለ የኮምፒውተር ሃርድዌር ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም። ይህን ነገ ሳስብ ሁሌም ወደ አእምሮዬ የሚመጣ ድሮ ልጅ እያለሁ ያየሁት የሁለት ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ የተጓዙ ልዑል ወንድማማቾች ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን የማይረሳ ፊልም ይታወሰኛል። የፊልሙም ዕርዕስ “Coming To Amenrica” ይሰኛል። ታዲያ በታሪኩ ውስጥ የንጉሱ ልጅ እንዲያገባት ከቀረበችለት ሙሽራ ጋር በሰርጉ እለት ባህልና ስርአቱን ጥሶ ከታዳሚው ገለል አድርጎ ጥቂት ጥያቄዎችን ይጠይቃታል፤ እንዲህም ሲል “ምንድነው የምትወጅው?” እሷም በፍጥነት “አንተ የምትወደውን ሁሉ” ትለዋለች። ጥያቄውንም በመቀየር “ምን አይነት ነው የሙዙቃ ምርጫሽ?”፤ እሷም አሁንም በፍጥነት በመመለስ “አንተ ምርጫህ የሆነው ሙዚቃ ሁሉ” ስትል መለሰችለት። ታሪኩን ለማሳጠር ያህል ብዙ ነገር ቢጠይቃትም በተመሳሳይ ስትመልስለት ልቡ የተሰበረው ልዑል በመጨረሻም የእንሰሳትን ሁሉ ስም እየጠራ እንደነሱ እንድጮህ ቢነግራት ያለማቅማማት በመጮህ ወደሰርጉ አዳራች እንደ ሽዋዋ ውሻ እየዘለለች የገባችው ነገር እረሳለሁ እንኳን ለሚል ሊረሳ የሚችል አይደለም። እውነት ነው፤ ሰዎች የራሳቸው ማንነት ፈጽሞ ሳይኖራቸው እንደማየት አሳዛኝና ልብ ሰባሪ የሆነ ነገር የለም። ኤዲመርፊ ምስጋና ይግባውና የዚያን አፍሪካዊ ማህበረሰብ በእውርነት ተረግጦ የመገዛት ባህል ጥሩ አድርጎ በትወናው አንጸባርቆታል። በቃ፤ እውነታው ባይጥምም እንዲህ ነው። አሁን እንዳለው እንደኛ አይነት ማህበረሰብ አገናዝቦና አመዛዝኖ የገዢዎችን ትክክለኛነት ወይንም ክፋት ማወቅ በዛም መሰረት ምን እንደሚያደርግ መምከር ፈጽሞ የሚታሰብ አይሆንም። የማህበረሰቡ ንቃተህሊና ዝቅተኝነት እንዲሁምና መሃይምነት ተጨምሮበት፤ መንግስት ለነሱ በውስጡ
  • 12. Samuel Lakew 12 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ተመችቷቸው እንደሚዋኙበት ያለ የሞቀ ባህር ሆኖላቸዋል። አንድ ቀን ባህሩ እንደሚቀዘቅዝ ወይንም ጭራሽ ደርቆ ምድረ በዳ እንደሚሆን ከቶውንም አይከሰትላቸውም። ከሆነም በኋላ እንኳን ቢሆን እውነትን ለመቀበል ይቸገራሉ። በምቾታቸው ወቅት መንግስት ለነሱ እንደ አምላክ ነውና ያለ ነበረና የሚቃወሙት ሁሉ የሰይጣን እና ተከታዮቹ ጭፍራዎችን ሆነውና ተመስለው ይታዩዋቸዋል። ማንኛውም ከገዢው መንግስት የሚነገሩ ነገሮች ሁሉ ከእምነት መጻህፍት ይልቅ ይታመናሉ፤ ተቀብለውም ያንኑ መልሰው ያስተጋባሉ። የተግባርም ሆነ የሃሳብ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ናቸው። እነዚህን ዝርዝር ችግሮችና የታቀዱ እንዲሁም የታለሙ የስነ ልቦና ጥቃቶች (mind control ወይም brain wash) ባልገባን ሁኔታ እኛም ማህበረሰቡን እና ወካዮቻቸውን፤ የአንደበቱንም ገላጮቹ ግብዝና አደርባይ እያልን ስም ብንሰጣቸውም፤ ይህ እንዳለ ሆኖ ነገሩ ግን ከዛም ያለፈና የላቅ መሆኑን መፍትሄው ላይ መስራት ለሚፈልግ በጎ ምሁር ሁሉ ይህንና ማንኛውንም ተዛማጅና ተያያዥ ነግሮችን አጥርቶ መገንዘብ ይገባዋል ብዬ አምናለው። በአጠቃላይ ስለማህበረሰብ ስናወራ የምናስበው ወይንም አያይዘን ልናየው የሚገባ ትልቁ ምስል እነዚህ እስከ አሁን ያየናቸውን ነገሮችና ሌሎችንም ተጨማሪ አካተን መሆን ይገባል። ገዥው መንግስትም ሆነ ደጋፊዎቹ እንዲሁም ቀሪውም ማህበረሰብ አንድ ላይ የዚህ የትልቁ ማህበረሰብ አካል ናቸው። እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ትክክለኛና ከምንም የጸዳ የትምህርት እድል ባላገኙና ንቃተ ህሊናቸውም ባልዳበረ ማህበረሰብ አንድ ጊዜ የሚመራቸው መሪ ከተጣመመ እጅግ አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ። የመጣውን ሁሉ አሜን ብሎ መቀበል ልማዱ ነውና። እንዲህ ያለው ህዝብ ጥሩ መሪ ይፈልጋል። ብልህና አስተዋይ መሪ ያስፈልጋቸዋል፤ ልክ በጎች ጥሩ እረኛ እንደሚያስፈልጋቸው ያለ፤ ከተኩላ የሚታደግ ብርቱ እረኛ ለምስኪን እና ደካሞቹ በጎች እንደሚያስፈልጋቸው ሁሉ። እረኛው ቢለግም ግን እሱን ከመከተል ውጪ ምንም ማድረግ የማይችሉት በጎች መጨረሻቸው የተኩላዎች ሲሳይ የመሆናቸው ጉዳይ ሳይታለም የተፈታ ነገር ነው። እንደ በግ ለመኖር የወሰነ ማህበረሰብም የመኖርና ያለመኖር ዋስትናው በመሪው ላይ ብቻ የወደቀ ነው። ታዲያ እንዲህ ያለው ህዝብ ምንም እንኳን ግራና ቀኝ አይቶ ባይራመድም፤ በመልካም መንገድ ከተመራና ከተኮተኮተ የዘመናዊና ሳይንሳዊ የሆነ ተግባር ከውነው አገርን ባይቀይሩም ፤ እንደ ወታደር የተባሉትን እና የታዘዙትን ካመኑበትና ከሰለጠኑበት በኋላ ሊተገብሩት ስለሚችሉ ቢያንስ አይራቡም፤ አይጠሙም። አገር በጠላት ቢወረር እንኳን፤ እንደ አምላክ ቃል የሚሰሙት መንግስታቸውን በመሆኑ ከጥሩ መሪ ጋር ሳይሰስቱ ህይወታቸውን በመለገስ በጀግነት ተዋድቀው አገርን መታደግ ይችላሉ። አባቶቻችንም በጥበብና በእውቀት ታግዘው ይህን አድርገዋል፤ እያስተማሩም አንቅተዋል። መልካምንም ባህልና ልምድ ለማህበረሰቡ እያወረሱ የሀገር ፍቅርን እና ስብእናውን አጎልብተዋል። የማይታመነውንም ከውነው በክብር አልፈዋል። እኔም ሳስባቸው ዛሬን ባለማየታቸው ታድለዋል ብዬ አልኩ። “የአቤ ጉበኛ ህመም” “ጥቅምን ሲያሳድድ ሊደርስ የሚችለውን የማይጠገን አደጋ እያዩስ እነሱም ለምን ይታወራሉ?” በተቃራኒው ደግሞ አሁን በኢትዮጵያ እያየን እንዳለው የተኩላ ባልንጀራ የመሰለ ገዢ ሲገጥም፤ የመጨረሻው ሰው ቁጥር እስኪቀር ድረስ አራጃቸውን ያለማስቀየም የያንዳንዳቸውን ቤት አንኳክቶ እንኪመጣ ተራቸውን ይጠብቃሉ። እንደ በግ በፈቃደኝነትም ህይወታቸውን ይለግሳሉ። በተቃርኖ የሚቆሙ፤ ከማህበረሰቡ የተሻሉና የነቃ አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች ይህን እብደት አይተው ሊያነቋቸው ቢፍጨረጨሩም፤ ማህበረሰቡ ግን ፍላጎቱ ዋጋ የሚሰጠውን እሴት ለመጠበቅም ሆነ ለማግኘት ምርጫው መገዛት ነውና የገዛ ማሰቢያ ጭንቅላቱን መብላቱ አደጋው ሳይታየው አሳቢዎቹንና ድምጾቹን አሳልፎ ለአውሬው ገዢ ይሰጣቸዋል። ይህም ነገር ሲደጋገም፤ የገዥዎችም ጭካኔ ሲበረታ ለሃገሪቷ ተስፋ ሊሆኗት የሚችሉ የተሻሉ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተመናመነ ይሄዳል። እምነትና
  • 13. Samuel Lakew 13 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 እስተሳሰባቸውም እንዲሁም ዘራቸው ጭምር እንደዛው አብሮ ይጠፋል። ታዲያ በህይወት ለመቆየት ካለው አደገኛነትና ምቹ አለመሆን ሳቢያ ከሞት ያመለጠ ገሚሱም ለስደትና እንግልት ይህወት ይዳረጋል። ህዝብና መንግስትም እንደ እናትና የመጨረሻ ልጅ አይነት ሆነው የእሹሩሩ ህይወት ይቀጥላል። መንግስትም ተብዬው ሲያሻው በጠዋት ገድሎ ልብ ይሰብራል፤ ከሰአትም ተመልሶ ለቅሶ ደርሶ ልባቸውን ይጠግናል። አዎ፤ ልብ እንደዚህ መቀለጃ ሆኗል። ሞኝ ህዝብ እና አረመኔ መንግስት ሲገናኙ የሚሆነው ይኸው ነው። ምንም እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የመንግስት ሃላፊዎች በተዋረድ የማገናዘብ ብቃትና ንቃተ ህሊና (cognitive ability7 ) እጦት ሰለባ ቢሆኑም ትንሽ ብቻ ከሚገዙት ማህበረሰብ በያዙት ስልጣን ሳቢያ በመሻላቸው በግድ እያሳመኑም ሆነ እያወናበዱ መግዛት ይችላሉ ማለት ነው። እነዚህ መሪዎች በጉልበት እንጂ በሃሳብ መግዛትና መምራት ስለማይችሉ በማህበረሰቡ ውስጥ የተሻለ ግንዛቤ ላላቸው ጥቂት ግለሰቦች ሃሳባቸውን መሸጥ አይችሉም። ማንኛውም አይነት የአስተሳሰብ ብልጫና በሃሳብ ልቀት ምክንያት የተጠቁ የሚመስላቸው እነዚህ ባለጊዜ ነን ባዮች ሰዎች በተመሳሳይ ሁኔታ በሃሳብ የላቀ ምላሽ መስጠት፤ ሃሳብንም በሃሳብ ማሸነፍ ስለማይችሉ አጠቃን ብለው የሚያስቡትን ግለሰብ ወይንም ቡድን አልያም ያጠቃቸው ከመሰላቸው ግለሰብ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሌሎች ግለሰቦችም ሆኑ ቁሶችን በመፈለግና ኢላማ በማአድረግ የበቀላቸው ገፈት ቀማሽ ያደርጓቸዋል። ይህን በማድረጋቸውም ከሚሰማቸው የአደጋና የጥቃት መንፈስ በመላቀቅ የአሸናፊነት ስሜት እንዲሁም ስልጣን በነሱ እጅ ብቻ እንደሆነ ለሚነግራቸው ውስጣዊ የክፋት ድምጽ ተግዢ በመሆን ለጊዜው ቢሆን እፎይታን ነማግኘት ትንሽ ተንፈስ ይላሉ። እንዲህ ያለውም ባለብዙ ፊት የሆነው፤ የተዛባው ጎስቋላ ስብናቸው፣ አቋማቸውና ማንነታቸው የማይገባቸውን ስልጣን ጨብጠው እስከቆዩ ድረስ ለተቺዎቻቸውና ተቃዋሚዎቻቸው እጅግ እደገኛ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። ጠላት ብለው የሚፈርጁትን ማንኛውንም ግለሰብ ወይንም ቡድን ከቅጣቱ እስኪማር በዚህ መልክ ያሰቃዩታል ወይም ቶርቸር ያደርጉታል። ይህም ተጎጂውና በቀል የሚሰነዘርበት ግለሰብ ወይም ቡድን በቃ እስካላለ ድረስ ጥቃታቸው በደጋፊዎቻቸው ጩኸት እየታጀበ ያለማቋረጥ ይቀጥላል። ለተጎጂዎችና ሰለባዎችም ከምንም በላይ ትናንት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ታገልን ሲሉ ከነበሩ ሰዎች የዚህ ክፋት ተባባሪ እንደመሆን የሚያም ነገር የለም። ይህን ህመም “የአቤ ጉበኛ ህመም” ብዬ እጠራዋለሁ። ይህንንም ለምን እንዳልኩ ጥቂት ዘለቅ ስትሉ ሁሉም ይገለጥላችኋል። ደራሲው አቤ ጉበኛ በደርግ ጊዜ የማህበረሰቡን የዋህነትና ሞኝነት እንዲሁም የገዥዎችን ክፋትና የደጋፊ አጨብጫቢዎቻቸውንም ታሪክ በመልካም ብዕሩ ከትቦ ባያስቀርልን ኖሮ የእሱ እይታ ምስክርነት ከወዴት ይገኝ ነበር እያልኩ ትንቢታዊ መሰል ጽሁፎቹን ለዘመኑ አስደናቂ ማስረጃ ነውና ብደብቀው ታሪክም እንዳይወቅሰኝ ጥቂት ልጠቅስ የግድ ሆነብኛል። የሁለት ዘመን አንድ ማጣቀሻና ማስረጃ! አቤ ጉበኛው በ 1965 ዓ/ም ከፍተኛ ትምህርቱን ለመከታተል ቢሄድም ከአመት በኃላም በመፈንቅለ መንግስቱ ምክንያት ለውጥ መቷል ሲሉት ሁሉን ትቶ ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: አቤም በ1966 ዓ/ም ሁኔታውንም ታዝቦ ይህን በማለት በገዛ ብዕሩ የሚከተለውን ከትቦ ነበር:: 7 Cognitive ability በጎግል ፍቺ መሰረት “የግንዛቤ ችሎታ” ሲል ይፈታዋል። በእውቋ የስነልቦና ተመራማሪ Linda Gottfredson [12] ትርጓሜ መሰረት ደግሞ፤ የእውቀት (ኮግኒቲቭ) ችሎታ በአመክንዮ የማሰብ ፣ እቅድ የማውጣት ፣ ችግሮችን የመፍታት ፣ በጥልቀት የማሰብ ፣ ውስብስብ ሀሳቦችን የመረዳት ችሎታ ፣ በፍጥነት መማር እና ከልምድ መማርን የሚያካትት የአእምሮ ችሎታ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። [Cognitive ability may be defined as a mental capability that … involves the ability to reason, plan, solve problems, think abstractly, comprehend complex ideas, learn quickly and learn from experience.] "በአገራችን ላይ የለውጥ እንቅስቃሴ መጀመሩን ሰማሁ፡፡ ከሰማኋቸው ወሬዎች በተረዳሁት መሠረት ሁኔታው መልክና አቅጣጫ የሌለው ወደ ደም መፋሰስ የቀረበ ሆኖ ታየኝ፡፡ ወደ አገሬና ወደ ቤተሰቤ ተመልሼ ሞቱንም ሽረቱንም ከአገሬ ሕዝብ ጋር ከመካፈል የበለጠ ተገቢ ዕድል እንደሌለኝ በማመን ወደ አገሬ የምመለስበትን ቀን ለማፋጠን ወሰንሁ፡፡ የጥናቱን ባይሆንም ከጉብኝት ጊዜዬ ቀሪውን አቋርጬ ወደ አገሬ ተመለስሁ።” [13]
  • 14. Samuel Lakew 14 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 የተከብረው አቤ ጉበኛ ታዲያ አገር ቤት ገብቶ ሁኔታውን ሁሉ ቢመለከት ጊዜ ለውጥ የሚሉት ነገር እንደኛ እንደ እሁኑ ዘመን የልጅ እቃቃ ጨዋታና ነፋስ ማባረር አይነት መሆኑ ገባው:: ትችቱንና ተቃውሞውንም በጋዜጣ መጻፉን ቀጠሎ ነበር:: የደርግ ስልጣኑን በሃይል መቆጣጠሩ አልጥምህ ያለው አቤ ታዲያ በቀልድ እያዋዛ መልእክቱን በቲያትር መልክ ፅፎ ለታዳሚዎቹ ያቀርብ ነበር:: ከድርሰቶቹም ውስጥ "ፖለቲካና ፖለቲከኞች" የተሰኘው በዋናነት ይጠቀሳል:: ሰዎች አቤ የሚፅፈውን ነገር ሁሉ እየተከታተሉ ፖለቲካ ነው የሚጽፈው በማለት የዘመኑ የደርግ አጨብጫቢዎች ቁም ስቅል ያሳዩት ነበር። መተቸትና የማይሆነውን መቃወም ዛሬ የተጀመረ አይደለምና፤ እንደኛው እንዳሁኑ ዘመን ያሉ የደርግ ታማኝና እርኩስ ቡቹሎችም የሚፅፈውን አይወዱለትም ነበር:: ታዲያ እንደዛሬ አፋጣኝ መልስ የሚሰጥበት ቲውተር ወይንም ፌስቡክ ያልነበረበት እንዲሁም ያልታለመበት ዘመን በመሆኑ እቤ በጋዜጣው እድሉን በመጠቀም ለተቃውሟቸውና ክሳቸው እንዲህ ሲል እስከ እሁንም እጅግ ገራሚ የሆነ መልስ መስጠት ግድ ሆኖበት ነበር። አዎ፤ በ 1955 ዓ/ም የተደረሰው “አልወለድም” እና የበርካታ መጽሃፍቶች ደርሲ አቤ ጉበኛ የዘመኑ ነብይ ነበር:: አቤ ትንቢተኛ ነበር:: የዛው ዘመን ነቀዞች ተቃዋሚዎቹና አስገዳዮቹ ዛሬም አፍርተውና ተባዝተው ፤ ፍትህና ጥበብ ጠል ዘራቸውንም ከትውልድ ትውልድ አውርሰው እነሆ አሁንም እነሱ አእምሮ አልባ ሆነው ሌላውንም የነሱ አምሳያ አድርገው በመቅረጽ ወደ ወድቀታቸው አንደርድረው ከጣሏቸው ከራረሙ:: አቤን አትተንፍስ እንዳሉት እኛንም ዛሬ ይሉናል:: አቤ ትንቢተኛው ብዕርተኛ እንዳለውም ሆነና ዛሬም ለሰባዊነት፣ ለፍትህና ለዲሚክራሲ ታግለናል እያሉ በአደባባይ እየደሰኮሩ ሲያደነቁሩን የከረሙት ሊቅ እና ምሁር ነን ባዮች ዲሞክራሲ ያሉትን ትቼ ፍትህንና ሰባዊነትን ከሚያዋርዷት ጋር እነሆ በፍቅር ወድቀው በአይናችን በብሌኑ ተመልክተን ለመታዘብ በቃን:: አንሶላም ተጋፈው እርኩሰታቸውን ፈፅመው ሲያበቁ የኛዎቹም ጉዶች እነ ግርማዊ ጭጭ ይበሉና እነ አፈ-ንጉሥ አይተንፍሱ እኛኑ መልሰው በመቃወም "ሰው ሲሞት አትቃወሙ፤ ፀጥ በሉ። ለናንተም ሆነ በህይወት ላሉትም አይበጅም:: የናንተ ተቃውሞ ነው ግድያውን የሚያባብሰው" በማለት ህሊና ቢስነታቸውን እና ፀረ-ሰብአዊ አቋማቸውን ሳይደብቁ እያሳዩን ‘በሰው ቁስል . . .’ እንደሚሉ የቆሰለውን ልባችንን እየነካኩ እንዲመረቅዝ ማድረጉን ተያይዘውታል። "ይህ ቲያትር የተጻፈው የምንም ዓይነት ፍልስፍና ማስፋፊያ ወይም መቃወሚያ እንዲሆን አይደለም። ዋና አላማው የአገራችን ለውጥ ተጀምሮ እየገፋ በመጣበት አንድ ጊዜ ላይ የታየውንና አሁንም ባንዳንድ ሰዎች ላይ የሚታየውን ቅሌትና አሳሳችነት ለሕዝብ ገልጾ ለማሳየትና ፍርዱን ለባለ ጉዳዩ ሕዝብ ለመተው ነው፡፡ ... ከእነዚህ ሰዎች አንዳንዶቹ ከግል ትችት አልፈው በጋዜጣ፣ በመጽሔት፣ ወረቀት በመበተን ለማሳጣት ሞክረዋል፡፡ ሰሚ ቢያጡ እንጂ “ፀረ ሶሻሊስት፣ ፀረ አብዮት፣ አድሃሪ” ሲሉኝ (መንግስት) ምን እንዲደረግብኝ መፈለጋቸው ኑሯል? በነሱ ቤት አንድ ሰው ምንም ያህል ለሀገሩ ጠቃሚ ይሁን፣ ምንም ያህል ወገኖቹን ይውደድ በእነርሱ አስተሳሳብ ካልተስማማ መኖር የማይገባው ሰው ነው፡፡ . . . አንዳንድ ሳዲስቶች (በሰው ስቃይ የሚደሰቱ ጉዶች) እንደሚመኙት ከወገኖቼ በአንዱ እጅ ብሞት እንኳ በዚያ ዕብድ ጭካኔ የብዙዎች ወገኖቼን ቅን መንፈስ ለውጬ አላየውም፡፡ ያለኝን ያህል ችሎታና ዐቅም ካስፈለገም ሕይወቴን ጭምር ለሀገሬ ከማበርከት ከቶውንም ወደኋላ አያሰኘኝም፡፡ ...አሁን ችግር የሆነብን በአገራችን ሁኔታዎች ላይ የምንመለከታቸውን ችግሮች እንዳንወያይባቸው ለምን ትንፍሽ ብላችሁ ማለታቸው ነው፡፡ ለመሆኑ እነግርማዊ ጭጭ ይበሉና እነ አፈ-ንጉሥ አይተንፍሱ እንደሚመኙት ሁሉ ሥልጣን የነሱ ቢሆን ኖሮ ምን ሊሠሩ ኑሯል? ለነጻነት ለዕኩልነትና ፍትህ ስንታገል ኖርን የሚሉ ሰዎች ለምን ሀሳብን በመጨቆን ያምናሉ? ጥቅምን ሲያሳድድ ሊደርስ የሚችለውን የማይጠገን አደጋ እያዩስ እነሱም ለምን ይታወራሉ? እኔ ግን ማንም ዋሾ ይጥላኝ እንጂ ያየሁትን መግለጼን መተውን እንደከፍተኛ ሀገርን መካድ ስለምቆጥረው ያየሁትን እውነት በቀልድ መልክ አቅርቤላችኋለሁ፡፡" [14]
  • 15. Samuel Lakew 15 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 የአደርባይነት ልካቸው፤ በድሃው ህዝብ ሞት፤ ዘሩ አማራ ነው እየተባሉ በህጻናቱም መታረድ የመሳለቃቸው ነገር ሁሉ አንድ ላይ ሲታይ ከአቤ ዘመን ይልቅ የአእምሮ መጨንገፉም ሆነ የሞራል ልዕልናው በብዙ ጎልብቶ መላሸቁ አሁን የሚያስፈራ ደረጃ ላይ መድረሳችንን አመላካች ማሳያ ነው። ያኔም የነበረው አደርባይነት አሁንም ተባብሶ አድጎ አለ። ያኔ አቤ በ“አልወለድም” ድርሰቱ የተረከው የህዝብ አእምሮ ማጣት፤ የገዢዎችም አረመኔነትና ነገን የሚያይ አዙሮ ማሰቢያ ማጣት የደመነብስ ተጓዥነታችንን ያጋልጥብናል። አቤም ለነገ ሳይል ይህል ብሎ በ”አልወለድም” ድርሰቱ ልቦለድ አስመስሎ እምቁን ስሜቱን በመጻፍ ተነፈሰው። ገጸ ባህሪያትንም ፈጥሮ በራሱ አንደበት ትንቢትን አናገራቸው። ሁሉም እውነት ነበረ። በጊዜና ቦታ የማይወሰን እውነት! እንዴት የአቤ ጽሁፍ መልእክቶች ሁሉ የኛን ዘመን አጉልተውና ቁልጭ አድርገው ሊያሳዩ ቻሉ? ይህ የዘወትር ጥራያቄዬ ነው። ለራሴም ዘወትር የምመልሰው መልሴም ዘመን ተቀየረ እንጂ አየሩም ሆነ ህዝቡ ያው ነው የሚል ነው። ማህበረሰቡ እራሱን በራሱ እያየና አምሳያውን እየተካ ቢያልፍም መንፈሱና አስተሳሰቡ ግን እንዳላለፈ ማሳያ ነው። እነ አቤ ጉበኛ እና መሰል ጓደኞቹ ግን ዛሬ በመንፈስም በስጋም የሉም። ብዙዎቹ ዘራቸውን እስኪተኩ አልተጠበቁም። አዎ፤ እነሡማ አይናቸውን በአይናቸው እንዲያዩ አልተፈቀደላቸውም። እነሱ የአስተዋይና እና የጥበበኛ ሰዎች ዘር እንጂ የብሄርና ጎሳ ዘር የላቸውምና፤ ከማንም በላይ ልቀው ለክፉዎች፣ ለደካማ ሸውራሮችና ለጨለምተኞች ስልጣን ላይ መቆየት ስጋት በመሆናቸው እየተሳደዱ በዘመናት ሁሉ እስከአሁኗ ሰአት ይታደናሉ። ይገደላሉ። ዘርና ጎሳ እንዲሁም የአንባገነኖች ድንፋታ አይገባቸውምና አምርረው ይጠሏቸዋል። ጥበባቸውንና እውቀታቸው እንደ ክፉ መንፈስ ቆጥረውባቸው እያስቆጠሩ ዘራቸውን ያጠፉታል። የአእምሮተኞች ዘር ማጥፋት ዘመቻም ዛሬም ድረስ ገዥዎች ትኩረት ሰጥተው በትጋት የሚሰሩበት ጉዳይ መሆኑ ለዚያ ነው። ለደናቁርት መሪዎች ይህን ሲያደርጉ ከዛሬ ይልቅ ነገ እየተሻለ የሚሄድ ይመስላቸዋል። እውነትን እንደመሰላሸው በስሜታቸው ይለኳታልና ህይወታቸው በስህተት የተሞላ ነው። አያስተውሉምና ከስህተታቸውም አይማሩም። ከአውሬም በላይ አውሬ አለና፤ ከህሊና ቢስ በላይ ህሊና ቢስ ሞልቷልና ኮትኩተው ያሳደጓቸው ጨካኝ አዞዎች አንድ ቀን ፊታቸውን እስኪዞሩባቸው ብቻ ይሆናል የእድሜ ገደባቸው። የአቤ ጉበኛን ‘አልወለድም’ መጽሃፍ አባቴ በትንሿ ሼልፍ ለአቅመ ንባብ እስክበቃ ደርድሮ ከቆየኝ መጽሃፍቶች ውስጥ አንዷ ነበረችና ሁሉም ባይገባኝም፤ ያነበብኳት ግን ገና በጠዋቱ ነበር። ለዛም ይሆን አላውቅም አንዳንዴ “አዲስ ወታደራዊ መንግሥት በሚሰብክበት ጊዜ ህዝቡ በየቦታው ተስፋውን እየተመገበ ይፈነጭ ነበር፡፡ በየጊዜው ወደከተማ ስመላለስ እንዳየሁት ሕዝቡ አዲሱን መንግሥት ያላንዳች መቃወም ተቀብሎት ነበር፡፡ የባላገሩ ኗሪም ምንም አልተቀንቀሳቀሰም ነበር፡፡ ነገር ግን ከጊዜ በኋላ አንድ ሁለት ዓመት ቆይቶ በገበሬው በነጋዴው በባለ ኢንዱስትሪውና በሌላውም ሠርቶ ኗሪ ህዝብ ላይ ግብርና ቀረጥ እየተደራረበ ለጦር አለቆች መቀማጠያ ለጦር መሣሪያዎች ማደርጃና ማብዣ ሆነ፡፡ የሕዝቡም ጠቅላላ ኑሮ ሰላም ከማጣቱና መንሰራፊያ ከመሆኑ በቀር ከድሮው በምንም አልተሻለ፡፡ ... ለሥልጣንና ለሹመት የሚመረጡት የጦር መኮንኖች ብቻ ስለሆኑ ስንቱ አዋቂ በንግድና በእርሻ ሥራ ራሱን ለመርዳት ካልሆነ በቀር በመንግሥቱ ድርጅቶች ገብቶ የሥራ ተካፋይ ለመሆን ዕድል አጣ [15]። የኛዎቹ አዲስ መንግሥት መሥራቾችም በኃይል ጭጭ አድርገው እየገዙን እያየን ‘አገራችንን ከጭቆና አገዛዝ ወደ ነጻነት መራናት’ እያሉ ይፎክሩብናል፡፡ ይኸውም የጊዜውን ነፋስ በመከተል ነው፡፡ ... ለውጡ የትኛው ነው? እናንተ ለውጥ ብላችሁ የምታምኑት የጥቂት ሀብታሞችን መሞትና መንገላታት ነው? እኛ የምንፈልገው እንዳይጎዱንና እንዳያጠቁን እንጂ እነሱ ቢሞቱ ደማቸውን አንጠጣው፤ ቢሰቃዩና ቢንገላቱ የመንፈስም ሆነ የአካል ደስታ አናገኝበት! ወይስ መሻሻል የምትሉት ሲቪል ሹም ሽሮ ወታደራዊ ሹም መሾሙን ነው? ወይስ ከሕዝብ አንዱ ድምጽ ሊሰጥበት የማይችለውን ለስሙ ግን የህዝብ መንግሥት (ሬፑብሊክ) የሚባል መንግሥት መቋቋሙን ነው? ኧረ ለውጥ የምትሉት የቱን ነው? ድርብ ቀረጥና ግብር መክፈሉን ነው? ጠቃሚ ድርጅቶችን እያደከሙ ለውጭ ጠላት እንኳ ሳይሆን ያገርን ሕዝብ ለማጥቃት የጦር ድርጅቶችን ማስፋፋቱን ነው? እንግዲህ አዲሱ መንግሥት ያሳየን ለውጥ ይህን ነው፤ ይህን ከሆነ መሻሻል የምትሉት ሌላ ነገር ነው [16]፡፡
  • 16. Samuel Lakew 16 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ሳስበው ልክ ከአቤ ጉበኛ ጋር በዚያ ዘመን በአንዳች ሃይል ጊዜውን አዛብቼ፤ ከጊዜው ቀድሜ አልያም እሱ ወደ እኔ ጊዜ መቶ የመከረኝና አልወለድምን ሲጽፍ ያማከረኝ፤ አብሬውም የጻፍኩም ይመስል የክስተቶቹ አዲስ አለመሆን ይገርመኛል። ክስተቶች ያው ናቸው። ሰዎችም እንደዚያው። ጊዜዎች ግን ያምታታሉ። አንዴ 1950ዎቹ፤ ሌላ ጊዜ ደሞ 1960ዎችና ሰባዎች፤ መልሶ ደሞ አሁንና 1990ዎች። ክስተቶቹ የመጀመሪያቸው አለመሆናቸውን፤ ቀድመውም በህይወቴ እንደሆኑ ያለ ያለመገረም ስሜት ይሰማኛል። ለዚህ ነገር ገላጭ የሆነው ቃል ከፈረንሳውኛ በስተቀር በሌሎች ቋንቋዎች አይገኝምና ጠቁሜችሁ ልለፍ። ቃሉ ‘ዴዣቮ’ ወይንም በፈረንሳይኛ ሲጻፍ (déjà vu8 ) ይሰኛል። የአእምሮ ጄኖሳይድ (Intellectual Genocide) በኢትዮጵያ በመጨራሻም፤ ያነሳኋቸውን ነገሮች በአእምሯችን ይዘንና ጨምቀን፤ አንድ ላይም አያይዘን አንዱን ካንዱ ሳንነጣጥል ብናብላላቸው እንደሚከተለው ወደ መደምደሚያችን መንደርደር እንችላለን። በነዚህ የጠቀስኳቸውና ያብራራኋቸው አመክንዮአዊ ሙግቶቼ መሠረት ከሄድን እንግዲህ የዚህ የኦነጋዊ መር የኦሮሙማ መንግስትም ሆነ የቀድሞው የወያኔ መር መንግስት ቁጥር አንድ ጠላት ምሁሩ ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም። አሁንም ግልጽ ለማድረግ ያህል፤ ምሁሩ ስል የነቃ መንፈስ ያለው፤ የተማረው፣ ከብዙሃኑ የተሻለ ክፉውንና ደጉን ለይቶ የሚያስብ፣ ምን እየተከወነ እንደሆነ የሚያውቀውና የሚከታተለው፣ ለምን እና እንዴት ብሎ የሚጠይቀው፣ የሚተቸው፣ የሚወቅሰው፤ የገዢዎችን ወንጀል የሚያጋልጠውና ለአገርና ለህዝብ ደህንነት የሚጨነቀውን ክፍል ማለቴ ነው። እናም ከብሄር ይልቅ በባሰ መልኩ ምሁርነት የነዚህ እና የቀደሙት ጥቂት የአገዛዝ ስርአት ተቀዳሚ ጠላቶች ነበሩ፤ ዛሬም ናቸው እያልኩ ነው። ‘ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው’ እንደሚሉት ብልሆቹ አባቶቻቸን፤ እነዚህ ሰዎች የሚፈሩት የሚጠሉት የሚያወራን፣ የሚጽፍን፣ ማስረጃን በፎቶና ካሜራ የሚያስቀርን፣ ሂሰኛንና ተቺን፣ ወንጀላቸውን ለአለም የሚያጋልጡትን ወዘተ ነው። ለዚህም ማስረጃ ለመጥቀስ የቀድሞው ሟች ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በ1993 ዓ/ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአንድ ጊዜ 42 የሚሆኑ የሃገሪቱን ምርጥ ምሁራን ፕሮፌሰሮችን እና ዶክተሮችን ጠራርጎ ማባረሩና ብዙዎችንም እያሰረ ማሰቃየቱ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው [18]። ወያኔ መሩ የቀድሞው ኢህአዲግ የተሻለ የተባለውን የትምህርት ስርአቱን በተመሳሳይ ሁኔታ መግደሉና ማበላሸቱ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱንም የዚህ የዘር ተኮር የጎሳ ፖለቲካው አይዲዎሎጂ ፕሮፓጋንዳ ማስፋፊያና ማሰልጠኛው ማድረጉ ዛሬ የደረስንበት እጅግ ወደባሰው የማህበረሰብ የሞራል ልእልና አንዲሁም አስተዋይነት መሞት፤ በዚሁም ሳቢያ ለመጣው የሃገር ውድቀት ትልቁን ድርሻ ይደስዳል። በተመሳሳይ መንገድም የመለስን ህልም ተርጓሚውና ራእይ አስፈጻሚው፤ የስም ለውጥ ብቻ ያደረገው አብይ አህመድ ክፉኛ ታሞ የነበረውን የትምህርት ስርአት ሙሉ በመሉ በመግደል አፈር የማልበስ ስነስርአት ላይ ይገኛል። ለዚህ ማሳያ ይሆን ዘንድ አንድ ትንሽ ተራ ማሳያ ብቻ እንኳን ብናይ፤ አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት ባሳየው የህክምና ባለሙያዎችን የማራከስ፣ የመናቅና የማንቋሸሽ ተግባሩ የዚህን መንግስት ባስ ያለ ፀረ ምሁርነትና ፀረ-ትምህርት አቋም መገለጫው ያደረገ መሆኑን ነው። ታዲያ ማህበረሰቡ በሽታውን እንኳን ለሚያክሙት ሃኪሞች አለመሟገቱና እንዳልሰማ አንዳንዴም እንደ ወንጀለኛ አይቶ ማለፍ በነሱ ላይ መፍረዱ የገዢዎች መሳሪያነቱን ያመላክተኛል። ማህበረሰባችን ደጋግሜ አንዳሉት እውነትን አመዛዝኖ መያዝና ለነገ ማቀድ መገለጫው ባለመሆኑ፤ ስጋቱን እና ውድቀቱን አይተው ሊያድኑት ህይወታቸውን አስይዘው ከገዢው መንግስት ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ሲተናነቁላቸው የነበሩትን፤ በአማራው ተወላጅና የኦርቶዶክስ አማኞች ላይም እየመጣ የነበረውን የዘር ፍጅት አደጋ እቅድ ሲያጋለጡ የቆዩትን እንደ እስክንድር ነጋ ያሉ የነጻነት ታጋዮችና ጀግኖች ያለምክንያት በግፍ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ በእስር ቢቆዩም፤ 8 Déjà vu (Noun): A feeling of having already experienced the present situation. (Oxford Dictionary)
  • 17. Samuel Lakew 17 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ከላይ በዘረዘርኳቸው ምክንያቶች እስራቸውን እና ግፋቸውን ለምን ብሎ የሚጠይቅላቸው ተቆጪ ማህበረሰብ እንደሌላቸው ሲታይ እጅግ ልብ ቢሰብርም፣ ቢያሳዝንም፣ ሊገርመን ግን አይገባም። ‘ለአዲስ አበባና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ከፍለው እያለ፤ የማህበረስቡ መልስ ለምን ዝምታ ሆነ?’ ብለው ለሚገረሙና እስክንድር ነጋ እና አስቴር ስዩም (ሁለቱም ሰዎች እስከዚህ ቀን 05 ጃንዋሪ 2021 ድረስ በኢትዮጵያ እስር ቤት ሳይፈረድባቸው ታስረው ላይ ይገኛሉ) ለሚጠይቁ ግለሰቦች አሁንም መልሱ ይኸው ከላይ እንደተገለጸው ከውስን ግለሰቦች በስተቀር ማህበረሰቡ በፍርሃትም ይሁን በመስማማት ፈቅዶና ወዶ ከገዚዎች ጋር ማበሩና መተባበሩን በዝምታ መግለጹ ነውና፤ ይህንን አምኖና ተቀብሎ ማህበረሰቡን ከከባድ እንቅልፉ ለማንቃትና ለመቀስቀስ የተሻሉ መንገዶችን ተመካክሮ መዘየድና መፍትሄ መፈለግ ተገቢ ነው ስል ምሁራንን አጥብቂ እመክራለሁ። የመንግስት ተቺ እና ተቃዋሚ ለሆነ ሰው እንደ 1930ዎቹና እንደ 1940ዎቹ የምስራቅ የጀርመን ወጣቶች አይነት (ከ10 የቤተሰብ አባል ምስራቅ ጀርመኖች 6ቱ የመንግስት ጆሮ ጠቢ ነበር) ስጋቱ ከማህበረሰብም አድጎ ወደ ቤተሰቡ ጭምር መድረሱ አይቀሬ ነው። የመንግስት ቁንጮ ላይ ያለው ግለሰብ በህዝብ መገናኛ ሚዲያዎች አስተውሎ ለሚያዳምጥ ሰው ለወላጆችም ጭምር በልጆቻቸው ላይ ተፅዕኖ እንዲፈጥሩ በሚያስደርግ አስገዳጅ የፕሮግራም ቃላት (mind control) የታጨቁ መሆናቸውን ይገነዘባል። በአጠቃላይ ሲታይ እንግዲህ፤ እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ ከገጠመን እንዲህ ካለ ውስብስብና እጅግ ጥልቅ አዘቅት ገደልና ጨለማ ለመውጣት የሚረዱን ችግር ፈቺዎች ያስፈልጉናል። ችግሮችን የሚፈቱልንን አቅም ያላቸውን ማንኛውንም አይነት ሰዎች እኔነታችንን በመተው በትእግስና በትህትና ወርደን በመፈለግ አብረንናቸው ልንሰራ ይገባል። መሪውን ልንሰጣቸው ይገባል። በዘር ሳይሆን በውቀትና በተሻለ ባሰበ ስንመራ፤ ሁላችንም እንደየመክሊታችን ልንሰራና የአቅማችንን አስተዋጽኦ በማድረግ አገርን በትብብር አሳድገን በሰላም ለመኖር መወሰን ትልቁ ማስተዋል ነው ብዬ አምናለው። እስክንድር ነጋን እና መሰሎቹን እየተቃወመ እስክንድርን ካልሆንኩ ለሚለኝ ቅናተኛ ሰው አትችልም ከማለት ወዲያ ምን እለዋለው? እንደ እስክንድር ነጋ ያለ ድፍረት፣ አርቆ አስተዋይነትና እኔነት አልባ ሆኖ ለሌሎች ያደረ መሆን መኖሪያውን እስር ቤት ቢያደርግበትም፤ ከአምላክ የተሰጠው ነውና ይህን ለመሆን አይጥርም። እኛም የውስጣችንን እስክንድር እንፈልገውና ለሌሎች ብልህና አስተዋይ ሆነን እንኑር። በየሙያ መስኩ ያሉ ልሂቆቻችንን ካልተንከባከብን መጨረሻችን እንደሶሪያና አፍጋኒስታን እንደ ጀመርነው ተበላልተን እንዳንጠፋ እንጠንቀቅ። የተከፋፈለች አገር ልኡዋላዊነትን ጠብቃና አስከብራ መኖት አይቻላትም። የሱዳን ወረራና የመንግስት ዝምታ ለኢትዮጵያ መውደቅ አመላካች ነገሮች ናቸው። ዝምታ ደሞ ትርጉም አለው። መሬቱ ተሽጦ
  • 18. Samuel Lakew 18 Psychology – Science topic RESEARCH GATE: 05 January 2021 ORCID: 0000-0001-7272-1470 ወይም አገሪቷ እንዳለች እንደቁም ከብት በቁሟ ተሽጣ ሌሎች ቢያዙባትስ ምን ይታወቃል። ነገ ደግሞ ማን መሬት አለኝ ብሎ ይመጣና ይወረን ይሆን? የቻለውን ሁሉ ዘርፎ መገብጠልንም ምርጫው አድርጎ በሚያስብ የወራሪ መንፈስ ተላባሽ መንግስት እንዴት ተአማኒ ይሆናል? የምናየውንና የምንሰማውን ሁሉ ወስዶ ማገናዘቡና ተገቢውን ውሳኔ መወሰኑ ለመኖር ህልውና ወሳኝ ነው። የሁላችንም እኩል መጠለያና መኖሪያ የሆነች አገር እንደምታስፈልገን ገብቶን ከሆነ፤ ትንሽ የምናስተውና አርቀን መጪው ማየት የቻልን ሁሉ ስንሰማ ያደግናቸውን አእምሯችንን ያላሸቁትን የዘረኝነትና የጥላቻ ፈጠራ የፕሮግራም ትርክቶች (brain washing) ወደጎን በመተው መነጋገርና ወደ መግባባት በመምጣት አገርን እና ወገንን ወደ ማዳን ወስነን እንቁረጥ ብዬ እኔ በዚህ ጽሁፌ በታናሽነትና አክብሮት ዝቅ ብዬ የሚመለከታችሁን ሁሉ፤ የተከበሩ አንባቢዎቼንም እንዲሁ ጨምሮ እጠይቃለሁ። ከኛ የሚጠበቀው በበጎ ህሊናና በቅንነት መደማመጥ፣ መስማማትና መተማመንንም ወዘተ ብቻ ነው። እስከዛሬ እንዳለው በሽታችን ያለ ነገር፤ “እኔ ብቻ ልሰማ፤ እኔ ብቻ ልደነቅ፤ እኔ ብቻ ልታይ፤ እኔ ብቻ ልስራው፤ ከዚህም ጋር ተያይዞ የሚመጣውን ጥቅማ ጥቅም ሁሉ እኔ ወይም እኛ እናግኝ ምክኛቱም ተራዬ ነው፤ ጊዜዬ ነው፤ ከባለጊዜው ጋር ልመሳሰል፤ ለሚታረደው ምን አገባኝ ወዘተ” የሚል በበዛበትና ድንቁርና በነገሰበት በዚህ የአገራችን የጨለማ ወቅት እንደ እስክንድር ነጋ ያሉ ሰዎችን በባትሪ ፈልጎ ማግኘት ከዛሬ ነገ እጅግ እየከበደ ይሄዳል ብዬ አስባለሁ። የወደፊቷ ኢትዮጵያ መኖር ከቻለችና ከወደቀችበትም መነሳት እንዳለባት ካመንን ማገናዘብና ማሰብ የሚችሉ፤ ንቃተ ህሊናቸው የላቁ፤ ምንም ይሁን ምን ለዚህ ለማይደግፋቸው ማህበረሰብም ቢሆን ችግሩን ተገንዝበው እራሳቸውን እንደ መስዋእት በግ በማቅረብ ከሞት ጋር የሚተናነቁ ሌሎች እስክንድሮችና መስከረሞች (መስከረም አበራ)፣ ሌሎችም እንደ ኢንጂነር ይልቃሎች እና ልደቱ አያሌዎች ብዙ ብዙ ያስፈልጉናል። ሌላውን እንኳን ማድረግ ባንችል አቅም ያላቸውን እንደሚያስፈልጉን በማመን አስተዋይነትን መግለጽ ብልህነት ነው። ማዕበል ሲነሳ ብቻ መርከቧ እንዳጸምጥ እውነተኞዙን የየሙያ መሪዎች እያለቀሱ መፈለግ ሁሌም መፍትሄ አይሆንም። ማዕበል ሳይኖርም እንዲመሩን እንፍቀድላቸው። ይህን ባናደርግ ግን አንዳንዴ ድንገት ከተፍ የሚለው ማእበል ሁላችንንም ጠራርጎን እሊሄድ እንደሚችል አሁን እናስብ። ለሚታረዱት ምስኪን የአማራ ተወላጆች ዛሬ ሎቻችንም በጊዜ ሳይረፍድና ወደኛም ሳይመጣ እንጩህ፤ እንቃወም። ብንችል ከሰባዊነትም እንጻርና ቃሉ እንግዳ ቢሆንብንም የአንድ ሀገር ዜጎች እንዳላቸው የብሄራዊነት ስሜት ጤነኛ መተሳሰብ ኖሮን አንድነታችንን እናጠንክር። አንድነት ማለት የትርክቱ ‘አሃዳዊነት’ ሳይሆን ትርጉሙ እንደዚህ ባለው ወቅት፤ የውስጥም ሆነ የውጪ ወራሪዎች ሲከቡን ብቻ የምንረዳው ነገር ይመስለኛ። በአማራ ህዝብ ላይ እየሆነ ያለው ጭፍጨፋና ጥቃት አሳዛኝ ነው። አሁንም አማራን ለማጥቃት በሚመስል መልኩ አገሪቷን አብይ አህመድ በሱዳን ጓደኛው አማካኝነት አስወርሮ ለአማራው በክልሉም ጭምር ሲኦል እየሆነበት መቷል። ከክልል ውጪም ያለው አማራ ላይ የዘር ጭፍጨፋው ቢቀጥልም የአማራ መሪዎች ዝምታን መርጠዋል። ሞት እንደሚመጣ ይሰማል፤ እርምጃ ግን አይወስድም። ወረቀት አስተካክሎ መክተት እንደተሳነው ሰው አይነት፤ አማራም ሁለቱንም አማርጮች፤ ወይ መሸሽ አለዚያም እራሱን መከላከል እንኳን ከብዶት እንደበግ መታረጃ ካራው እየተሳለለት እያየና እየሰማ እንኳን ለመታረድ ቀኑን ይጠብቃል። በየቀኑም መታረዱን ለምዶታል። ወከልኩት የሚለውም የአማራው ብልጽግና ፓርቲ ተብዬውም እጅግ ዘገምተኛ የሆነ፤ ለመንግስት የተገዢነትና የባርበት ካዳበረውን የልማድ ሱሱ ሊላቀቅ ባለመቻሉ በተመሳሳይ የማህበረሰቡ አሉታዊ እምነቶችና ባህሎች ተቋዳሽ የሆነ የችግሩ አካልም ሰለባም በመሆኑ ነገሮች የተወሳሰቡ መስለዋል። ከነሱ ወደተሻሉት ጥበበኞች ሄደው እርዳታ ይጠይቃሉ ወይስ በባርነት ይቀጥላሉ የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚታረደውን የአማራ ደም ያስቆም ወይም ይባስ ያስቀጥል ይሆናል። መለስ ዜናዊ ማሰብ የሚችሉ ብልሆችን ፈፅሞ አጠገቡ እንደማያስደርስ ያለፈ ታሪክ ቢሆንም ይህን መረዳት የዛሬውን የፈነዳዳ የችግር ቁልል ለመገንዘብና መፍትሄ ለማምጣት እጅጉን ተቃሚ ነገር