AcR-PP-Amh.ppt of higher institution for each
- 1. ክፍል አንድ
የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ምንነትና አይነቶች
I የጥናትና ምርምር ክፍሎች
ጥናትና ምርምር በሁለት ክፍሎች ይከፈላሉ
መሰረታዊ ጥናትና ምርምር
ተግባራዊ/የመስክ ጥናትና ምርምር/
መሰረታዊ ጥናትና ምርምር ፅንስ ሃሳበዊ ሆኖ አብዛኛዉን ጊዜ
በቤተ ሙከራና ከስራ ጋር በቀጥታ ያልተያያዘና ወዲያው
ተግባራዊ የማይደረግ ሊሆን ይችላል::
ተግባራዊ ጥናትና ምርምር- በተጨባጭ በሚከሰቱ ልዩልዩ ችግሮች
ላይ የሚያተኩርና የችግሮችን መንስኤ በመለየት መፍትሄ
ለማገኘት የሚጥር የምርምር አይነት ነዉ፡፡
- 2. II የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ምንነት
• ምርምር ማለት በዘፈቀደ የሚሰራ ሳይሆን ሳይንሳዊ መንገድን
በመከተል መርጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን ወደ አንድ
መደምደሚያ የሚያደርስ መሳሪያ ነዉ፡፡
• ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በእለት ከእለት የማስተማር ስራ
አፋጣኝ መፍትሄ ለሚፈልጉ እና በተግባራዊ የስራ ሂደት ላይ
ለሚያጋጥሙ አካባባቢያዊ (የት/ቤት፤ የክፍል ዉስጥ፤ የተማሪዉ፤
የመምህሩ ወ.ዘ.ተ…) ችግሮች ችግር ፈቺ በሆነ አካባቢያዊ መፍትሄ
በመስጠት የተማሪዎች የመማርና የመስተማር ዉጤት መሻሻል
ላይ ያለመ ምርምር ነዉ፡፡
- 3. III የተግባራዊ ጥናትና ምርምር አይነቶች
ሀ. በግለሰብ ደረጃ በተናጠል የሚደረግ ተግባራ ጥናትና ምርምር
መምህሩ/ቷ በት/ቤት ወይም በክፍል ዉስጥ የሚታዩ ችግሮችን
ለማጥናት የሚጠቀሙበት የአጠናን ዘዴ ሊሆን ይችላል፡፡
ለ.የትብብርጥናትና ምርምር
ምሳሌ፡- ከኮሌጅ መምህራን ጋር በመተባበር መስራት
ሐ. ት/ቤት አቀፍ
መ. ወረዳ አቀፍ ወዘተ በቡድን ከሌሎች ጋር መስራት
- 4. IV የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ጠቀሜታ
• ሙያዊ ብቃትን ያጎለብታል፤
• ችግሮችን የመፍታት ክህሎትን ያዳብራል
• ሙያዊ ፍቅር እንዲኖር ያግዛል፤
• በተግባር የሚያጋጥሙ ችግሮችን በስራ ተነሳሽነት ለመፍታት
ያስችላል
• በስርአተ ትምህርቱ ያሉትን ችግሮችን የበላይ አካላት እንዲገነዘቡ
ለማድረግ ይረዳል
• እንደ ልማድ የተወሰዱና በልምድ የሚሰሩ ነገሮች እንዲሻሻሉና
እንዲቀየሩ ያደርጋል
• የምርምሩን ግኝት ወዲያወኑ በስራ ላይ በማዋል ለዉጡን
ለመገምገም ይረዳል
• የሙያ እድገትን ለማስገኘት ይረዳል
• አብሮ የመስራትን ባህል የዳብራል
• ት/ቤትን የመለወጥ አቅምን ያሳድጋል
• የራስን ስራ ውጤታማነት ለማወቅ ይረዳል ወዘተ፡፡
- 5. V የማስተማር ስራና የምርምር ስራ ግንኙነት
• እዉቀት መስጠትና ማመንጨት የተሻለ እንዲሆን ማስቻል
• የት/ት ጥራትን ለማስጠበቅ
• የመረጃና የልምድ እጥረትን ለማስወገድ
• የተለያዩ የት/ቤት ችግሮችን ለመፍታት
• ሰው ለውጥ ፈላጊና ጠያቂ ፍጡር በመሆኑ
• ዕውቀት ቋሚ አይደለም ያድጋል፤ይሰፋያል ፤ይለወጣል
ወ.ዘ.ተ በመሆኑ የማስተማር ስራ በጥናትና ምርምር ስራ
መታገዝ አለበት
- 6. VI የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዋናዋና ባህረያት
• ቅጽበታዊነት (immediate)
• ኡደታዊነት (recycling)
• አሳታፊነት
• ቅንጅታዊነት
• አይነታዊ
• ጽብረቃ
• (ችግር፡ ምርመር፡ መፍትሄ፡ ትግበራ ያካትታል)
- 7. VII ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ወሰን
ተግባራዊ ጥናትና ምርምር የግለሰብን ችግር ከማጥናትና መፍትሄ
ከመሻት ጀምሮ እስከ አንድ የትምህርት አደረጃጀት ድረስ ሊያጠና
የሚችል ነው፡፡ ለምሳሌ በትምርት መስክ የአንድ ተማሪ ችግር
ከአንድ መምህር ማስተማር ዘዴ ጀምሮ በክፍል፤በሴክሽን፤በት/ቤት
ደረጃ ብሎ እሰከ ወረዳ ድረስ ሊጠና የሚችል ነው፡፡
- 8. VIII የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ስነ-ምግባር
• ከግለሰቦች አድሎና ፍላጎት የፀዳ መሆን አለበት
• ከሚመለከታቸው አካላት ተቀባይነት ሊኖረው ይገባል
• በማንኛውም ሰዓት አስተያየት መቀበልና መፈፀም
• አንዳንድ ዶክመቶችን ለመፈተሽ ፈቃድ ማግኘት ይጠበቅበታል
• ከመታተሙ በፊት ውይይት ሊደረግበት ይገባል ወ.ዘ.ተ
- 9. ክፍል ሁለት
ለስራ ላይ ምርምር ረዕስ መምረጥና የምርምሩን
ፕሮጀክት ማቀድ
• የተግባራዊ ጥናትና ምርምር የአሰራር ቅድመ ተከተል
• I ችግሩን መለየት (problem identification)
• ያሉትን ችግርች በደንብ ማየት ቢቻል መዘርዘር
• ችግሮች፤ ምሳሌ፡-
– የተማሪ ባህሪ ችግር
– ተማሪው ለትምህር ያለው ፍላጎት አናሳ መሆን
– የተማሪዎች ተሳትፎ አናሳ መሆን
– ተማሪ ውጤት ዝቅተኛ መሆን
– የመረጃ መሳሪያ ችግር
– ጥያቄና መልስ የክፍል ተሳትፎ ዝቅተኛ
– ንባብ ችሎታ ዝቅተኛ
– የስነሰረዓት ጉድለት
- 10. ርዕሱ ከስራ ጋር ተያያዥ መሆኑን ማረጋገጥ / መማርና
ማስተማር ጋር/
• መነሻ ሀሳቦችን መገምገም
• ከተግበራ ስፋት (scope for action)
• ተገቢነት(relevance)
• ምጥነትና(manageability)
• ተዛማጅነት(compatibility)
• –አጭርና ግልጽ
• –በአጥኚው በኩል መጻፍ
ምሳሌ፡-
• (How I can ------)
• ምሳሌ፡- የ------- ክፍል --------- ተማሪዎችን የባህሪ ችግር እንዴት
እፈታዋለሁ?
- 11. II. ችግሩን መግለፅና መተንተን/reconnaissance and
analyzing the situation/
• ሀ. የጥናቱን ዳራ ማስቀመጥ (background of the study)
• ምሳሌ፡-
ባህሪ ማለት ምን ማለት ነው ?
• ተማሪ ሊያሳይ የሚችለው አላስፈላጊ ባህሪያት ምንምን ሊሆኑ
ይችላሉ?
• ይህ ችግር ብዙውን ጊዜ ይከሰታል? በየትኛው እድሜ ገደብ?
• ለባህሪያቶቹ መከሰት ዋናዋና ምክንያቶች ምንድን ናቸዉ?
• ይሕ ባህሪ ተማሪዎችን ወደየት ሊመራ ይችላል?
• ስለዚህ የዚህ ጥናት ዋና አቅጣጫ ምንድነ ነው
- 12. ለ. ችግሩን ማብራራት/statement of the problem
• መሆን የነበረበት ምንድነ ነው? አሁን በግልፅ እየታየ ያለው ባህሪ
ዝርዝር ማስቀመጥ
• ለባህሪዎቹ መከሰት ዝርዘር ምክንያቶችን መጠቆምና ማብራራት
• የትኞቹ ወይም ስንት ተማዎች ይህንን ባህሪ እንደሚያሳዩ መጠቆም
• መቼ፤ለምን፤ ወይም፤ እንዴት ችግሩ እንደታየ መጠቆም
• በተጨባጭ ማለትም በማስረጃ ባህሪዉ ያመጣውን ችግር መግለፅ
• ችግሩ ባይፈታ ወደፊት ሊገጥም የሚችለውን ችግር ማብራራት
• ከዚያ መሰረታዊ የጥናቱ ጥያቄዎችን ማስቀመጥ /basic
questions of the research /
- 13. የቀጠለ
• ምሳሌ፡-1. በት/ቤቱ በተማሪዎች የሚታዩ የባህሪ ችግሮች ምንምን ናቸው?
• 2. በተማሪዎች ላይ የሚታዩ የባህሪ ችግር መንስኤዎች
ምንምን ናቸው?
• 3. እነዚህ የባህሪ ችግሮች ምን አይነት የመፍትሄ ሀሳቦች ተግባራዊ
መደረግ አለባቸው?
• ሐ. የጥናቱ አላማ
• የጥናቱን ዋናዋና ዓላማዎች ለይቶ መጻፍ
ምሳሌ፡-
1. የ---------- ተማሪዎች የባህሪ ችግር አይነቶችን መለየት
2. የባህሪ ችግርና መንስኤዎችን መለየት
3. ለሚታዩ የባህሪ ችግሮች መፍትሄ ሃሳብ መፈለግና በመፈተሸ ችግሩን መፍታት
- 14. መ. የጥናቱ አስፈላጊነት/significance of the study/
• በዚህ ጥናትና ምርምር የሚገኘው ውጤት ወይም ውጤቱንና
መፍትሄ ሀሳቡን በማግኘት መፍትሄ ለመስጠት የሚፈልጉ አካላትን
ለይቶ መጥቀስ
• ምሳሌ፡- - ለር/መምህሩና ሌሎችም ባለድርሻ ኣከላት
• - ለት/ቤቱ መምህራን
• - ተጨማሪ ጥናትና ምርምር ለማድረግ ለሚፈልጉ ሊሆን ይችላል፡፡
- 15. ረ. ሙያ ነክ ቃላት (operational)
– በጥናቱ ውስጥ የተጠቀሙበትን አዳዲስ ሙያዊ ቃላት ትርጉም
መስጠት
ለምሳሌ፡- ዲሲፕሊን -የስነስረዓት ማጉዋድ
• ቢጤዎች- አቻ፤
• እንቅፋት -መሰናክል ወዘተ
- 16. III የተዛማጅ ጽሑፍ ቅኝት (Review of Related
Literature
• በርእሱ ዙሪያ የተለያዩ ድርሳናትን መከለስ
ምሳሌ፡- ባህሪ ምንድን ነው ?
• የባህሪ ችግር አይነቶች
• ባህሪ እንዴት ይከሰታል
• የባሃሪ ችግር በመማር ማስተማራ ላይ የሚያሳድረው
ተፅዕኖ
• በባህሪ ላይ ተፅዕኖ የሚያደርጉ እነማን ናቸው? በሚሉት ላይ
ድርሳኔ ክለሳ ማድረግ ይቻላል፡፡
- 17. IV የመረጃ ምንጭ
• የመረጃ ምንጭ
ሀ. መጀመሪያ ደረጃ መረጃ ፡- ይህም በቀጥታ፤ በምልከታ፤ በመለካት፤
ለምስክርነት ወይም በቀጥተኛ ሪፖርት የሚገኝ መረጀ ነው፡፡
ለ.ሁለተኛ ደረጃ መረጃ ፡- ታሪካዊ ፅሁፎች፤ጋዜጣ፤ መጽሃፍት ወዘተ
ላይ የሚወሰዱ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
- 18. ሀ. የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች
• የፅሁፍ መጠይቅ
• የቃል መጠይቅ
• ምልከታ
• ፈተና
• ውይይት
• ከመዛግብት መረጃ መሰብሰብ ናቸው
- 19. የቀጠለ
• የጽሁፍ መጠይቅ - በጽሁፍ መልስ የሚሰጥበት
- ጠያቂና መላሽ በአካል ላይገናኙ ይችላሉ
- ጥያቄዎች ክፍት ወይም ዝግ ሊሆኑ ይችላሉ
- ዝግ ጥያቄ አማራጮች ይሰጣሉ
- ጥያቄዎቹ አጭር ፤ግልፅ መሆን አለባቸው
• የቃለ መጠየቅ - ሁለቱም ጠያቂና ተጠያቂ በግንባር የሚገኙበት
– በተለይ ማንበብና መፃፍ ለማይችሉ ሰዎችና ህፃናት ወዘተ
ምልከታ - ተሳትፎዊ፡-ተመራማሪው በቀጥታ እየተሳተፉ ምልከታ ሲያደርግ
ተሳስተፎ አልባ ምልከታ
• ፈተና፡- የተማሪዎችን እውቀትና ክህሎት በፈተና መለካት ይቻላል
ምሳሌ፡-አማርኛ የማንበብ ችሎታ መፈተን
ውይይት - ሊወክሉ የሚችሉ የተወሰኑ ናሙናችን በመጠቀም ሃሳብ መሰብሰብ
ከመዛግብት መረጃ መሰብሰብ፡- ለምሳሌ ከተማሪዎች ሮስተር፤ የተማሪዎች ዝርዝር
ካርድ /መዘገብ/ ወዘተ መረጃ መሰብሰብ
- 20. V የመረጃ ውጤት ትንተና ስልት
• የተጠኚዎችን ዳራ ማስቀመጥ
• የተሰበሰቡትን መረጃች በሰንጠረዥ ወይም በዝርዝር፤ በቁጥር
(በመቶኛ) ወይም በግልፅ መዘርዘርና ማብራራት
- 25. IX ፅብረቃ /reflection/
• በዚህ ወቅት የሚቀርበው በተግባራዊ ወቅት የተገኘው እውቀት፤
ልምድ ወይም ለውጥ ነው፡፡ ይህም በትግበራ ወቅት የተገኘውን
ውጤት በትክክል ለሌሎች ማሳወቅ /መግለጽ/፡